መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የጋብቻ ስነ-ስርአት

በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ ተወሰኑ የጋብቻ ስነ-ስርአቶች ትማራላችሁ።

1 አዲስ ተጋቢዎች ሊከተሏቸው የሚገቡ የጋብቻ ስነ-ስርአትን ታውቃላችሁ።2 እስልምና የደነገጋቸውን ጠቃሚ የጋብቻ ስነ-ስርአቶችን ታውቃላችሁ።

ከጋብቻ ጋር የተያያዙየህግ ድንጋጌዎች አንዳንዶቹ ከጋብቻው ውል በፊት የሚቀድሙ ፣ አንዳንዶቹ በውሉ ጊዜ እና አንዳንዶቹ ደግሞ ከውሉ በኋላ የሚፈፀሙ ናቸው። ባለ ትዳሮች ሊከተሉት ሚገባ የጋብቻ ስነ-ስርአትን የሚፈፅሙ ናቸው። ባለትዳሮች ሊከተሉት የሚገባ የጋብቻ ስነ-ስረአትን እስልምና አስገኝቷል። ይህ ሊሆን የሚገባው ከአሏህ ሽልማትን ለመቀበል በመፈለግ እና የትዳር ግኙኝነትን ለመጠበቅ እና ለማጠናከር ተስፋ በማድረግ ነው።

1 ኒያ (ማሰብ)

1 ኒያ (ማሰብ) በእስልምና ውስጥ ትልቅ ቦታ አለው። ተከታዩ ሐዲስ ለዚህ ትልቅ ማስረጃ ነው። ‹‹የስራዎች ሽልማት መሰረቱ ማሰብ ነው።›› ሁሉም ሰው ባሰበው ነገር ላይ ሽልማቱን ያገኛል።›› (ቡኻሪ 1 ፣ ሙስሊም 1907) ሆኖም ጥንዶቹ በጋብቻ ውስጥ መልካምን ነገር አስበው መግባት አለባቸው። ከአሏህ ብዙ ትሩፋት እና ሽልማት ለማግኘት በመፈለግ ብዙ ቢያስቡ (ኒያ) ቢያደርጉ በላጭ ነው። አንድ ሰው በጋብቻ ውስጥ ሊኖር ከሚችለው በጎ ሃሳቦች (ኒያዎች) መካከል ጋብቻ የሚያበረታቱ ትዕዛዛትን ለመፈፀም ፣ አሏህን ብቻ የሚገዙ ዘሮችን ለማብዛት ፣ እራስን በጋብቻ ለመሰብሰብ እና ከፈተና ለመጠበቅ ወ.ዘ.ተ የሚሉት ናቸው።

2 በጋብቻ ሌሊት ሱናውን መከተል

١
1-በሚገናኛት ጊዜ ባል ለሚስቱ ገር መሆን።
٢
2-ባል የሚስቱ ግንባር ላይ እጅን አስቀምጦ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ያስተማሩንን ዱአ ማንበብ፡ ‹‹አሏህ ሆይ! የዚችን ሴት መልካም ነገር እና በእሷ ውስጥ የፈጠርከውን መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። ከተንኮሏ እና በእሷም ውስጥ ከፈጠርከው መጥፎ ነገርም በአንተ እጠበቃለሁ።›› (ኢብንማጃ 1918)
٣
3 አንዳንድ ሶሃቦች እንዳሉት ባል ከሚስቱ ጋር ሁለት ረከአ ሶላት መስገድ የተወደደ ነው።
٤
4 የግብረ ስጋ ግኙንነት ከማድረግ በፊትዱአ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህም፡ ‹‹በአሏህ ስም! አሏህ ሆይ! ከሸይጧን ተንኮል ጠብቀን። የምትለግሰንንም (ልጅ) ከሸይጧን ጠብቀው።›› (ቡኻሪ 3271 ፣ ሙስሊም 1434) ሴቷም ይህንኑ ዱአ ብታደርግ ችግር የለውም።
٥
5 ሃያሉ አሏህ ከከለከለው ነገር መራቅ ያስፈልጋል። በእርግጥ አንድ ሰው ሚስቱ የወር አበባ ላይ በምትሆን ጊዜና በመቀመጫዋ በኩል መገናኘትን እርም አድርጓል (ከልክሏል)።
٦
6 አንድ ሰው ከሚስቱ ጋር የግብረስጋግኙኝነት ፈፅሞ እንደገና መጀመር በሚፈልግ ጊዜ ሱናው ውዱእ እንዲያደርግ ያዘዋል። ‹‹አንዳችሁ ከሚስቱ ጋር የግብረስጋግኑኝነት አድርጎ እንደገና መጀመር ቢፈልግ ውዱዕ ያድርግ።›› (ሙስሊም 308)
٧
7 ወንዱም ሆነ ሴቷ የወሲብ ሚስጥራቸውን ለሌሎች ሰዎች መግለጥ የለባቸውም። የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹አሏህ ዘንድ በትንሳኤዋ ቀን ከሰዎች መካከል በጣም ክፉ ወንዱ ወደ ሚስቱ ሄዶ፤ እሷም ወደ አሱ መጥታ ሳለ ከዛም ሚስጥሯን የገለጠ ሰው ነው።›› (ሙስሊም 1437)

3 የጋብቻ ድግስ

የጋብቻ ድግስ የተረጋገጠ ሱና ነው። ምክኒያቱም አብዱ ረህማን ኢብን አውፍ (ረ.ዐ) ባገባ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለውታልና፡ ‹‹አንዲት በግ እንኳ ብትሆን ደግስ።›› (ቡኻሪ 2048 ፣ ሙስሊም 1427)

በድግስ ጊዜ መታሰብ ያለበት ነገር

١
1 ሃብታሞችን ብቻ በመጥራት መወሰን የለበትም። ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዳሉት ‹‹ከምግብ ሁሉ የከፋው ምግብ ሃብታሞች ብቻ ተጠርተው ድሆች ያልተጠሩበት ድግስ ነው። የድግሱን ጥሪ ያልተቀበለ ሰው አሏህ እና መልዕክተኛውን አልታዘዘም።›› (ቡኻሪ 5177 ፣ ሙስሊም 1432)
٢
2 ድግሱን በአንድ በግ ወይም ደግሞ የገንዘብ አቅም ያለው ሰው ከዚህም በላይ ማድረግ ይችላል። ነገርግን ሳያባክን መሆን አለበት።
٣
3 ከስጋ ውጭ በሆነ ነገር መደገስም የተፈቀደ ነው።

4 በሰርግ ሰአት የሴቶች መዝፈን

ጥሩ እና የተፈቀዱ ቃላትን በመጠቀም ከወንዶች እይታ እርቀው ድቤ እየደቡ መጫወት ለሴቶች የተፈቀደ ነው። ሌላ የሙዚቃ መሳሪያ መጠቀም ግን የለባቸውም። በዚህ የደስታ ጊዜ መጫወት እና መደሰት በእስልምና የተፈቀደ ነው።

5 በደግነት መኗኗር

ከተረጋገጡ የጋብቻ ስነ-ስርአቶች ውስጥ አንዱ ተፈላልጎና ተዋዶ ህይወትን በተገቢው መንገድ አብሮ መኖር ነው። ሆኖም በአሏህ ፈቃድ ውዴታቸው የደስታን ህይወት እንዲኖሩ ያስችላቸዋል። አሏህ እንዲህ አለ፡ ‹‹በደግነት ተኗኗሯቸው።›› (ሱረቱ ኒሳዕ 19)

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር