መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የመንገደኛና የህመምተኛ ሶላት

እስልምና ቀላል እና ችግርን የማስወገድ ሀይማኖት ሲሆን ይህም በህመም እና በጉዞ ላይ አንዳንድ የሶላትን ድንጋጌዎች ማቃለልን ይጨምራል። በዚህ ትምህርት በተጓዥ እና በሽተኛ ጸሎት ላይ ስላለው ፍርድ ትማራላችሁ።

በጉዞ ላይ ያለ ሰው የሶላትን ድንጋጌዎችን ማወቅየህመምተኛ ሰው የሶላትን ድንጋጌዎች ማወቅ

አንድ ሙስሊም አእምሮው ጤናማ እስከሆነ ድረስ በማንኛውም ሁኔታ ሶላት ግዴታው ነው። ነገር ግን እስልምና በሽታንና ጉዞን ጨምሮ የሰዎችን የተለያዩ ሁኔታዎችና ችግሮችን ግምት ውስጥ ያስገባል።

ለመንገደኛ ምን ይወደድለታል?

መንገደኛ ከቦታ ቦታ በሚዘዋወርበት ወይም ከአራት ቀን ላነሰ ወቅት ጊዚያዊ ቆይታ በሚያደርግበት ስፍራ ሆኖ ባለ አራት ረከዓ ሰላቶቹን ሁለት ረከዓ አድርጎ መስገድ ይወደድለታል፡፡ዙህር ዐሱርና ዒሻን የአገሬ ነዋሪ የሆነ ኢማምን ተከትሎ ካልሰገደ በስተቀር በአራት አራት ረከዓ ምትክ ሁለት ሁለት አድርጎ ይሰግዳል፡፡ እንዲያ ከሆነ ግን ኢማሙን ሊከተልና እንደሱ አራት ረከዓ ሊሰግድ ይገባል፡፡

ከፈጅር ሱና በስተቀር የተቀሩትን ተቀጥላ ሱና ሰላቶችን ቢተው ወይም ባይሰግድ ይችላል፡፡ የዊትርን ሶላት እና የሌሊት ሶላትን እንዲጠብቅ ተደነገገበት።

ዙህርና ዐስሩን በአንድነት መግሪብና ዒሻን በአንድነት አቆራኝቶ መስገድ ይችላል፡፡ በተለይ በሚዘዋወርበትና በሚሳፈርበት ወቅትና ሁናቴ ላይ ከሆነ የአላህን ህግ ገራገርነት እዝነትና ማጨናነቅ የሌለው መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡

የታማሚ ሰው ሰላት

መቆም የማይችል ወይም መቆም የሚያስቸግረው ወይም ለመቆም የሚያስችለው ፈውሱ የሚዘገይበት የሆነ ህመምተኛ ቆሞ መስገድ ይሻርለታል፡፡ እርሱ የሚሰግደው ቁጭ ብሎ ነው፡፡ቁጭ ማለትም ካልቻለ በጎኑ እንደተጋደመ ይሰግዳል፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡ ቁመህ ስገድ፡፡ ካልቻልክ ቁጭ ብለህ ስገድ፡፡ ካልቻልክ በጎንህ ተጋድመህ ስገድ አል ቡኻሪ 1066

የህመምተኛ ሶላት ህግጋት

١
ማጎንበስ (ሩኩዕ) ወይም ሱጁድ ማድረግ ያልቻለ ሰው በሚችለው ልክ ምልክት በማድረግ ይሰግዳል፡፡
٢
በመሬት ላይ ቁጭ ማለት የሚቸገር ሰው በወንበርናበመሰል ነገሮች ላይ ቁጭ ብሎ መስገድ ይችላል፡፡
٣
በህመም ምክንያት ለእያንዳንዱ ሰላት መጥራራት ወይም ዉዱእ ማድረግ የሚቸገር ሰው ዙህራና ዐሱርን በአንድነት መግሪብና ዒሻን በአንድነት በማቆራኘት መስገድ ይችላል፡፡
٤
ሰላት ለመስገድ በህመም ምክንያት ውሃን መጠቀም የማይችል ሰው በአፈር ተየሙም ማድረግ ይችላል፡፡

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር