መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት በሁለቱ ፆታዎች መካከል የግንኙነት ገደብ

በዚህ ትምህርት ውስጥ በአንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት መካከል ሊኖራቸው ስለሚገባ የግኑኝነት ደንቦች ትማራላችሁ።

1 በወንድ እና በሴት መካከል ሊኖር የሚገባው የግኑኝነት አደብ የሚቆጣጠረውን የሸሪአ የህግ ማዕቀፍ ጠቀሜታ ታውቃላችሁ።2 አንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት ቅርርብ ውስጥ የተደረጉ ገደቦችን ታውቃላችሁ።

የእስልምና ህግ በወንዶች እና በሴቶች መካከል ያለውን ቅርርብ ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሰዎች ጉዳዮች ላይ ትኩረት ይሰጣል። አሏህ ወንዶችን እና ሴቶችን የፈጠረው እርስ በእርሳቸው እንዲፈላለጉ እና እንዲሳሳቡ አድርጎ ነው። የዚህ ስበት እና መፈላለግ ውጤት ህጋዊ የሚሆነው በጋብቻ ብቻ ነው። የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ከእኔ በኋላ ለወንዶች ከሴቶች የበለጠ የከፋ ፈተናን አልተውኩም።›› (ቡኻሪ 5096 ፣ ሙስሊም 2741)

በወንድ እና በሴት መካከል ባለው ቅርርብ በጣም የከፋው እና አደገኛው ነገር ዝሙት ላይ መውደቅ ነው። ሸሪአ ይህን ስርአት ማጣት እና ግብረገብነት የጎደለው ተግባር መከላከል ብቻ ሳይሆን ወደ እሱ መቅረብንም በጥብቅ ከልክሏል። ሃያሉ አሏህ እንዲህ አለ፡ "ዝሙትን አትቅረቡ። እሱ በእርግጥ መጥፎ ስራ ነውና። መንገድነቱም ከፋ!" (ሱረቱ ኢስራዕ 32) ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አለ፡ ‹‹የአይን ዝሙት (የተከለከለን ነገር) ማየቱ ነው። የምላስ ዝሙት ማውራቱ ነው። እንዲሁም የውስጥ ፍላጎት እና ምኞቶች ናቸው። ሀፍረተ ገላዎች ይህን ሁሉ ይመሰክራሉ ወይም ይክዳሉ።›› (ቡኻሪ 6243 ፣ ሙስሊም 2657)

ማንኛውንም ስህተት እና ጥመት ለማስቀረት ሲባል እና መጥፎ ውጤት ከማስከተሉ በፊት በሴቶች እና በወንዶች ቅርርብ ላይ አስፈላጊ ሸሪአዊ ቁጥጥሮችን እና ገደቦችን አስቀምጧል። ለምሳሌ መግዛት ፣ መሸጥ እና ሌሎች የተፈቀዱ ግብይቶች እንዲሁም የግድ አስፈላጊ በሚሆን ጊዜ ሴት ዶክተሮች በማይኖሩበት ጊዜ አንዲትን ሴት ማከም ወ.ዘ.ተ ናቸው። ከእነዚህ ቁጥጥሮች እና ገደቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-

እይታን መስበር

አሏህ እንዲህ አለ፡ "(30) ለምዕመናን ንገራቸው! ዓይኖቻቸውን ያልተፈቀደን ከማየት ይከልከሉ፤ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፤ ይህ ለእነሱ የተሻለ ነው። አሏህ በሚሰሩት ሁሉ ውስጥ አዋቂ ነው። (31) ለምዕመናትም ንገራቸው! አይኖቻቸውን ይከልክሉ። ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ።" (ሱረቱ ኑር 30-31)

መነካካትን ወይም በእጅ መጨባበጥን ማስወገድ

አኢሻ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈችው እንዲህ አለች፡ መልዕክተኛውን የአብሮነት ቃልኪዳን ለሴቶች ገለፃ በተመለከተ ከተናገሩ በኋላ በአሏህ ይሁንብኝ የአሏህ መልዕክተኛ እጅ የአንዲትን ሴት እጅ ነክቶ አያውቅም።›› (ቡኻሪ 5288 ፣ ሙስሊም 1866) መቂል ቢን ያስር እንዳስተላለፈው የአሏህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፡ ‹‹አንድ ሰው ያልተፈቀደችለትን ሴት ከሚነካ የብረት ድዥኖ በአናቱ ቢገባ ይሻለዋል።›› (አጦበራኒ፡ አል-ሙጀም አል-ኪበር 486፤ አልባኒ ሰሂህ ብለውታል)

ሴት ጋር ብቻውን ተገልሎ መቀመጥ

የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ከመህረሙ ጋር ካልሆነ በቀር አንድም ወንድ ከሴት ጋር ብቻውን መሆን የለበትም።›› (ቡኻሪ 5233 ፣ ሙስሊም 1341) እንዲህም ብለዋል፡ ‹‹አንዳችሁም ከሴት ጋር ብቻውን አይሆንም ሶስተኛው ሸይጧን ቢሆን እንጅ።›› (አህመድ 115).......

በሴቶች ላይ የተጣሉ ገደቦች

ሙስሊም ሴቶች ከወንዶች ጋር የግድ መቀራረብ በሚያስፈልግበት ጊዜ ሊከተሏቸው እና ሊጠብቋቸው የሚገቡ ደንቦች እና ድንበሮች አሉ።

የሸሪአ የአለባበስ ስርአትን መከተል

ሙስሊም ሴት በመጀመሪያ የአሏህን ትዕዛዝ በማክበር እና ከዚያም ወንዶች እንዲያከብሯት እና በንግግራቸው ፣ በድርጊታቸው እና በእይታቸው እንዳይጎዷት ህጋዊ የሸሪአ የአለባበስ ስርአትን መከተል አለባት። አሏህ እንዲህ አለ፡"ለምዕመናትም ንገራቸው! አይኖቻቸውን ይከልክሉ። ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ። ጌጣቸውንም ከእሷ ግልፅ ከሆነው በስተቀር አይግለጡ። ጉፍታዎቻቸውንም በአንገታቸው ላይ ያጣፉ።" (ሱረቱ ኑር 31) አሏህ እንዲህም ብሏል፡ "አንተ ነብይ ሆይ! ለሚስቶችህ ፣ ለሴት ልጆችህም ፣ ለምዕናን ሚስቶችም መከናነቢያቸውን በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው። ይህ እንዲታወቁ እና (በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመሆን በጣም የቀረበ ነው። አሏህ መሃሪ አዛኝ ነው።" (ሱረቱ አህዛብ 59)

ወንዶች በሚኖሩ ጊዜ ሽቶ አለመነስነስ

የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፡ "ሰዎች ጠረኗን ያሸቱ ዘንድ ሽቶ ነስንሳ በሰዎች በኩል የምታልፍ ሴት ዝሙተኛ ናት አሉ።" (ሱረቱ ኒሳዕ 5126)

ሳይቅለሰለሱ ቆፍጠን ብሎ መናገር

አሏህ እንዲህ አለ፡ "የነብዩ ሴቶች ሆይ! ከሴቶች እንደማናቸውም አይደላችሁም። አሏህን ብትፈሩ ትበልጣላችሁ። ያ በልቡ ውስጥ በሽታ ያለበት እንዳይከጀል በንግግር አትለስልሱ። መልካም ንግግርንም ተናገሩ።" (ሱረቱል አህዛብ 32)

በጨዋነት እና በይሉኝታ (በሃያዕ) መራመድ

የሹአይብ ሴት ልጅ የአባቷን መልዕክት ለሙሳ (ዐ.ሰ) ልታደርስ በሄደች ጊዜ የነበረውን ሁኔታ አሏህ ስለ እሷ እንዲህ ይላል፡ "ከሁለቱ አንደኛይቱ ከሃፍረት ጋር የምትሄድ ሆና መጣች።" (ሱረቱል ቀሶስ 25) አሏህ ስለሴቶች ሲናገር እንዲህ አለ፡ ‹‹ከጌጦቻቸው የደበቁት ይታወቅ ዘንድ በእግሮቻቸው አይምቱ።›› (ሱረቱ ኑር 31)

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር