መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት ሽያጭ

በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ ሽያጭ ትርጉም እና ከእሱ ጋር ተያያዥ የሆኑ የህግ ውሳኔዎችን ትማራላችሁ።

1 የሽያጭ ሁክም ታውቃላችሁ2 የሽያጭን ህጋዊነት ጥበብ ትማራላችሁ3 የሽያጭ ቅድመ ሁኔታዎችን ታውቃላችሁ።4 ታስወግዷቸው ዘንድ የተከለከሉ የሽያጭ አይነቶችን ታውቃላችሁ።

የሽያጭ ትርጉም

በቋንቋ ደረጃ ሽያጭ ማለት አንድን ነገር በሌላ መለወጥ ነው። በህግ ደረጃ ደግሞ አንድ ሸቀጥ ከሌላ ሰው መገብየት ወደ ሶስተኛ ወገን መስተላለፍ ነው።

የሽያጭ ሁክም

ሽያች በቁርአን ፣ በሱና እና በኡለማኦች ስምምንት መሰረት የማይሻር ውል ነው። አሏህ እንዲህ አለ፡ "አሏህ ንግድን ፈቅዷል።" (ሱረቱል በቀራ 275)

የሽያጭ ጥበብ

1 የሰው ልጆች ሌሎች ሰዎች ያለ ክፍያ የማይሰጧቸው የሆኑ እንደ ምግብ ፣ መጠጥ ፣ ልብስ ፣ መጠለያ ቤት እና ሌሎች ሸቀጦችን ይፈልጋሉ። ሆኖም ሁለቱ ወገኖች ፍላጎቶቻቸውን የሚያሟሉት በሽያጭ ነው። ሻጩ የእቃውን የዋጋ ተመን ያገኛል። ገዡ ደግሞ የፈለገውን ሸቀጥ ያገኛል።

2 ሰዎች ህይወታቸው በተሻለ መንገድ እንዲመሩ ይረዳቸዋል። ምክኒያቱም የሰው ልጆች ፍላጎቶቻቸውን የሚያሟሉበት ምናልባት በሽያጭ ብቻ ነውና።

3 ሌብነትን ፣ ማጭበርብርን ፣ ስልጣንን ተገን አድርጎ ገንዘብብ መመዝበርን እና ሌሎች መሰል ተግባራትን ይከላከላል። ምክኒያቱም የሰው ልጆች በግዥ ፍላጎቶቻቸውን የሚያሟሉበት እድል አለና ነው።

የሽያጭ ምሰሶዎች

١
1 ሻጩ፡ የእቃው ባለቤት መሆን አለበት፡፡
٢
2 ገዡ፡ የገንዘቡ ባለቤት መሆን አለበት።
٣
3 የውል ቅፅ (ደረሰኝ)፡ የሻጩን ማቅረብ እና የገዥውን መቀበል ያካተተ መሆን አለበት።
٤
4 የሚዋዋሉበት እቃ፡ ዋጋው እና የሚሸጠው እቃ ነው።

የሻጭና ገዢ ቅድመ ሁኔታዎች

١
1 በአዕምሮው ጤነኛ የሆነ፡ አዕምሮው ጤነኛ ያልሆነ እና በሰካራም ሰው የተፈፀመ ሽያጭ ተቀባይነት የለውም።
٢
2 ለአቅመ አዳም የደረሰ፡ መረዳት እና ነገሮችን መለየት የሚችል ልጅ ዋጋው ትንሽ የሆነን ነገር መሸጥ ወይም አለመሸጥ ይፈቀድለታል። የሚሸጠው ነገር ከፍ ያለ ዋጋ ካለው እና ልጁ የመረዳት አቅሙ ከፍ ያለ ከሆነ እና እንዲሸጥ በሞግዚቱ ከተፈቀደለት ሽያጩ ተቀባይነት አለው። ነገርግን ነገሮችን የመረዳት ችሎታ በሌለው ህፃን ልጅ የተፈፀመ ሽያጭ ተቀባይነት የለውም።
٣
3- በህግ ያተገደአ መሆን
٤
4 ስምምነት እና ምርጫ፡ ተገዶ መሸጥ ፣ በቀልድ መልክ መሸጥ ተቀባይነት የለውም። ሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች በትክክል ወሸጥ ሳይፈልጉ ጭቆናን ወይም በደልን ፈርተው ከሆነ የሸጡት፤ ሽያጩ ተቀባይነት የለውም።
٥
5 ሻጩ ሸቀጡን (እቃውን) የማቅረብ ችሎታ ያለው መሆን፡ ይህን ማድረግ ካልቻለ ሽያጩ ተቀባይነት የለውም።

የውል (የሽያች እና የግዥ) መፈጸምያ (ገንዘብና እቃ) ቅድመ ሁኔታዎች

١
1 ዋጋው የሚታወቅ እና ከሚሸጠው ነገር መለየት፡ በእርግጥ ሽያጩ አንድን እቃ በአንድ እቃ መለወጥ ፣ አንድን እቃ በገንዘብ መለወጥ ወይም ደግሞ ገንዘብን በገንዘብ መለወጥ ሊሆን ይችላል። ሆኖም አንዱን ከሌላው መለየት አለበት።
٢
2 የሚሸጠው እቃ መኖር አለበት፡ ውሉ በሚፈፀም ጊዜ የሌለን ነገር መሸጥ አይፈቀድም።
٣
3 የሚሸጠው ሸቀጥ (እቃ) የተፈቀዳ መሆን አለበት፡ ነገር ግን የሚሸጠው ነገር አስካሪ መጠጥ ፣ የአሳማ ስጋ ፣ የሙዚቃ መሳሪያ እና ሌሎች ያልተፈቀዱ ነገሮች መሆን የለባቸውም።
٤
4 የሚሸጠው ነገር ንፁህ መሆን አለበት። ንፁህ ያልሆነን እና ንፁህ ሊያደርጉት ቢሞክሩም የማይፀዳ ነገር መሸጥ የተከለከለ ነው።
٥
5 ሸቀጡ ወይም እቃው በሻጩ እጅ መሆን አለበት። በሰማይ ላይ የምትበር ወፍን ወይም የተሰረቀ እቃን መሸጥ አይፈቀድም።
٦
6 እቃው የሻጩ ሰው ንብረት መሆን አለበት። የእሱ ያልሆነን ገንዘብ መሸጥ ለሻጩ ሰው አይፈቀድም። እንዲሸጥ ተፈቅዶለት ወይም ሃላፊነት ተሰጥቶት ካልሆነ በቀር።

የተከለከሉ ሽያጮች

١
1 ጉዳት ያለው ሽያጭ፡ ከተዋዋሉት ከሁለቱ ሰዎች አንዱን የሚጎዳ ሽያጭ ነው። ንብረቱን የሚያጣበት የሆነ ነው። ለምሳሌ ይኑር አይኑር የማያውቀውን ነገር መሸጥ ወይም ማቅረብ የሚችለውን መጠን ሳያውቅ ይሄን ያህል መጠን አቀርባለሁ ብሎ መሸጥን የመሰለ ነው።
٢
2 ጉዳት እና ማጭበርበር የታከለበት ሽያጭ
٣
3 አራጣ የታከለበት ሽያጭ
٤
4 በቀጥታ መሸጥ የተከለከለ ነገር መሸጥ፡ ለምሳሌ ሙቶ የተገኘ እንስሳ ስጋ ፣ አስካሪ መጠጥ ፣ የአሳማ ስጋ ወ.ዘ.ተ
٥
5 በምክን ያት መሸጥ የተከለከለ፡ ለምሳሌ ከጁምአ ሶላት ከሁለተኛው አዛን በኋላ መሸጥ እና በተፈለገበት አላማ የተከለከለ ሽያች፡ ለምሳሌ የወይን መጠጥ ለማውጣት የወይን ፍሬ መሸጥ እና ሰው ለመግደል ላሰበ ሰው ሰይፍ እንደ መሸጥ ያለ ነው።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር