መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የሮመዳን ጾም

የረመዷንን ወር መፆም አራተኛው የእስልምና መሰረት እና ትልቅ መሰረት ነው። በዚህ ትምህርት ስለ ፆም ትርጉም እና ትሩፋት እንዲሁም ስለ ረመዷን ወር ትሩፋት ትማራላችሁ።

የጾምን ትርጉምና ደረጃ ማወቅ።ስለ ረመዷን ወር ደረጃ ማወቅ።

አላህ (ሱ.ወ) ሙስሊሞች በአመት አንድ ወርን እንዲጾሙ ግዳጅ አድርጎ ደንግጓል፡፡ እሱም የተባረከውን የረመዳንን ወር ነው፡፡ አራተኛ የኢስላም ማዕዘንና ታላቅ መሰረት አድርጎታል፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- ‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደተፃፈ በናንተም ላይ ተፃፈ (ተደነገገ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡›› ይላል፡፡ (አል በቀራ 183)

የጾም ትርጉም

ጾም በኢስላም ያለው ትርጉም፡ ጎሕ ከቀደደበት ሰዓት ጀምሮ፣ ፀሐይ እስክትጠልቅ (የመግሪብ ሠላት አዛን የሚባልበት ወቅት) ድረስ ከምግብ፣ ከመጠጥ፣ ከግብረ ስጋ ግንኙነትና ከሌሎችም ጾምን ከሚያበላሹ ነገሮች እራስን በመቆጠብና በማገድ አላህን መገዛት ነው፡፡

የረመዳን ወር በላጭነት

የረመዳን ወር፣ በኢስላማዊው ቀመር ዘጠነኛው ወር ነው፡፡ ረመዳን ከዓመቱ ወራት ሁሉ በላጩ ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ከተቀሩት ወራት በበርካታ ነገሮች አልቆታል፡፡ ከነዚህ ብልጫዎች መካከል የሚከለተሉት ይገኙበታል፡፡

አላህ (ሱ.ወ) የተከበረውንና እጅግ የላቀውን መጽሐፍ -ቁርኣንን- በውስጡ በማውረድ የመረጠው ወር ነው፡፡

አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ብሏል፡፡-‹‹(እንድትጾሙ የተፃፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ፣ ከቅን መንገድና (ውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲሆን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡›› (አልበቀራ 185)

2 ረመዳን የጀነት በሮች ይከፈታሉ

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ረመዳን ሲገባ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ፤ ሰይጣናት ይታሰራሉ፡፡›› (አል ቡኻሪ 3103/ ሙስሊም 1079) አላህ (ሱ.ወ) መልካምን በመሥራትና ከመጥፎ በመራቅ ባሮቹ ወደርሱ የሚመለሱበትን ሁኔታ አመቻችቷል፡፡

ቀኑን የጾመና ሌሊቱን በመስገድ ቆሞ ያሳለፈ ሰው ያለፉት ወንጀሎቹ ይማሩለታል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹በእምነትና አላህ ዘንድ ያለውን ምንዳ በማሰብ የረመዳንን ወር የጾመ፣ ቀደም ሲል የሠራው ወንጀል ይማርለታል፡፡›› (አል ቡኻሪ 1910 /ሙስሊም 760) ‹‹በእምነትና አላህ ዘንድ ያለውን ምንዳ በማሰብ በረመዳን ወር (ተራዊሕና ተሃጁድን በመስገድ) የቆመ ሰው ቀደም ሲል የሰራው ወንጀል ይማርለታል፡፡›› (አል ቡኻሪ 1905/ ሙስሊም 759)

በረመዳን ውስጥ የዓመቱ ትልቅ ሌሊት ይገኛል፡፡

ይህች ሌሊት አላህ (ሱ.ወ) በመጽሐፉ፣ በዚች በርሷ ውስጥ የሚሠራ መልካም ሥራ፣ ለረዥም ዓመታት ከሚሠራ መልካም ሥራ እንደሚሻልና እንደሚበልጥ የተናገረላት ነች፡፡ አላህ (ሱ.ወ):- ‹‹መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺህ ወር በላጭ ናት፡፡›› ብሏል (አል ቀድር 3) እናም ይህችን ሌሊት በእምነትና አላህ ዘንድ ያለውን ምንዳ በማሰብ በመስገድ ቆሞ ያሳለፈ ሰው ቀደም ሲል የሰራው ወንጀል ይማርለታል፡፡ እርሷ በረመዳን ወር በመጨረሻዎቹ አስርት ሌሊቶች ውስጥ የምትገኝ ነች፡፡ ይህችን ሌሊት፣ ማንም ሰው በእርግጠኝነት በዚህ ዕለት ትሆናለች ብሎ መወሰንና መናገር አይችልም፡፡

የጾም ትሩፋት

ጾም በኢስላማዊው ሕግ የተደነገጉ በርካታ ትሩፋቶች አሉት፡፡ ከነዚህም መካከል፡-

1 ወንጀሉ ይማርለታል

በአላህ አምኖ፣ ትዕዛዙንም አክብሮ፣ በረመዳን ትሩፋት ዙሪያ የተላለፉ ጉዳዮችን እውነት ብሎ ተቀብሎ እንዲሁም አላህ ዘንድ የሚያገኘውን ምንዳ በመከጀል ረመዳንን የጾመ፣ ቀደም ሲል የሰራው ወንጀሉ ይማርለታል፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ረመዳንን፣ በአላህ አምኖ የሚያስገኝለትን ምንዳ አስቦና ከጅሎ የጾመ ሰው ቀደም ሲል የሰራው ወንጀል ይማርለታል፡፡›› (አል ቡኻሪ 1910 / ሙስሊም 760)

2 ጾመኛ፣ ከአላህ ጋር ሲገናኝ በመጾሙ ምክንያት በሚያገኘው ላቅ ያለ ምንዳና ጸጋ ይደሰታል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ጾመኛ ሁለት ደስታዎች አሉት፡፡ በሚያፈጥርበት ጊዜ የሚደሰተውና ከጌታው ጋር ሲገናኝ የሚደሰተው ደስታ ነው፡፡›› (አል ቡኻሪ 1805 /ሙስሊም 1151)

3 በጀነት ውስጥ ከጾመኞች በስተቀር ማንም የማይገባበት የሆነ ረያን የሚባል በር አለ፡፡

በጀነት ውስጥ ከጾመኞች በስተቀር ማንም የማይገባበት የሆነ ረያን የሚባል በር አለ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹በጀነት ውስጥ ረያን የሚባል በር አለ፡፡ የትንሳኤ ቀን ጾመኞችይገቡበታል፡፡ ከነርሱ ሌላ ማንም በርሱ በኩል አይገባም፡፡ የት አሉ ጾመኞች? ይባላል፡፡ ወዲያውም እነሱ ወደርሱ ይነሳሉ፡፡ ከነርሱ ሌላ ማንም በርሱ በኩል አይገባም፡፡ እነሱ ገብተው ሲያበቁ ይዘጋል፡፡ ማንም በሱ በኩል አይገባም፡፡›› (አል ቡኻሪ 1797/ ሙስሊም 1152)

4 አላህ (ሱ.ወ) የጾምን ምንዳ ወደራሱ አስጠግቶታል፡፡

እናም ክፍያውና ምንዳው፣ ከቸሩ፣ ከለጋሱና ከኃያሉ ጌታ ዘንድ የሆነለት ሰው ሊደሰት ይገባል፡፡ አላህ ባዘጋጀለትም ሽልማት ይበሰር፡፡ አላህ (ሰ.ወ) በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አንደበት ሲነግረን፡- ‹‹ፆም ሲቀር ሁሉም የአደም ልጆች ስራ ለራሳቸው ነው፤ እርሱ ግን የኔ ነው ምንዳውን የምከፍለው እኔው ነኝ፡፡›› ይላል፡፡ (አል ቡኻሪ 1805 /ሙስሊም 1151)

የጾም ሚስጥር

አላህ ሱ.ወ፣ በበርካታ ዓለማዊና መንፈሳዊ ምክንያቶች ጾምን ግዴታ አድርጓል፡፡ ከነዚህ መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል

1 የአላህን ፍራቻ ማጽናት

ጾም፣አንድ ባሪያ የሚወዳቸውን ነገሮች ወይም ፍላጎቶቹን በመተው፣ ስሜቱን በመጫን፣ አላህን የሚገዛበት አምልኮ በመሆኑ፣

2 ከወንጀልና ከሃጢኣት በመራቅ ላይ ስልጠናወይም ልምምድ መስጠት

አንድ ጾመኛ ሐላል ነገሮችን በመከልከል የአላህን ትዕዛዝ ማክበር ከቻለ፣ የወንጀልና የሀጢኣት ስሜቱን በመለጎሙና አላህ ከገደበው ወሰን በመጠበቁ፣የበለጣ ይመቸዋል

3 ችግረኞችን ማስታወስና መደገፍ

ጾም፣ የተራቡና የተቸገሩ ሰዎችን ሕይወት የሚካፈሉበትና ዓመቱን ሙሉ በችግርና በሰቆቃ የሚያሳልፉትን ድሆች ሁኔታ የሚያስታውሱበት የአምልኮ ዘርፍ ነው፡፡ ትክክለኛ የአላህ ባሪያ፣ ድሃ ወንድሞቹ ምን ያህል በረሃብና በጥማት እንደሚቸገሩ ያስታውሳል፤ በመሆኑም ለነርሱ የእርዳታ እጁን በመዘርጋት የሚቻለውን ሁሉ ያደርጋል፡፡

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር