መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የወላጆች መብት

በዚህ ትምህርት ውስጥ ወላጆችን ስለ ማክበር እና ከእሱ ጋር ተያያዥ የሆኑ ነገሮችን ትማራላችሁ።

1 ወላጆች በእስልምና ውስጥ ያላቸውን ደረጃ ታውቃላችሁ።2 የወላጆችን መብት ማክበር ታበረታታላችሁ፤ እነሱን አለማክበርን ታስጠነቅቃላችሁ።3 ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያላቸውን ሃላፊነቶች እና ግዴታዎች ታውቃላችሁ።4 ከወላጆች ጋር በሚኖራችሁ መስተጋብር ልትከተሏቸው ሚገቡ ስነ-ስርአቶችን ታውቃላችሁ።

የወላጆች ደረጃ በእስልምና

እስልምና ለወላጆች ትልቅ ክብር አጎናፅፏቸዋል። ክብራቸው በእስልምና ውስጥ በጣም ትልቅ ከሆነው የአሏህ አሃዳዊነት ጉዳይ ጋር አስተሳስሮታል።"ጌታችሁ እሱን እንጅ ሌላን አትገዙ። ለወላጆቻችሁም መልካምን ስሩ ሲል አዘዘ።" (ሱረቱል ኢስራዕ 23) ሃያሉ አሏህ ወላጆችን የወንድ እና የሴት ልጆች መኖር ሰበብ አድርጓቸዋል። ልጆች ያደረጉ ቢያደርጉ የወላጆቻቸውን ሃቅ መመለስ አይችሉም። ለልጆቻቸው ምቾት እና እንክብካቤ ሲሉ ያጋጠማቸው ፈተና ፣ ድካም እና መዛል ፣ ጉዳት ፣ እረፍት እና እንቅልፍ ማጣት እና እንግልት ሊክሱ አይችሉም።

ከአሏህ ፍትሃዊነት መገለጫዎች ውስጥ አንዱ ወላጆች ለልጆቻቸው ባደረጉላቸው ምስጉን ተግባራት እና እንክብካቤ በልጆቻቸው ላይ መብቶች ያላቸው መሆኑን መደንገጉ ነው። አሏህ እንዲህ አለ፡ "ሰውንም ለወላጆቹ መልካም አድራጎትን እንዲያደርግ አዘዝነው።" (ሱረቱል አንከቡት 8) እንዲህም አለ፡ "በቅርቢቱ አለም በመልካም ስራ ተወዳጃቸው።" (ሱረቱ ሉቅማን 15) በሌላ በኩል ደግሞ ከሶሃቦች አንዱ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ጠየቃቸው፡ የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሆይ! በጣም ላገለግለው የሚገባ ማነው? እሳቸውም፡ እናትህ አሉ። እሱም፡ ከዚያስ አላቸው። እሳቸውም እናትህ አሉት። ከዚያስ ማነው አላቸው። እሳቸውም እናትህ አሉ። እሱም ከዚያስ ማነው? አላቸው። እሳቸውም ከዚያ አባትህ አሉት።›› (ቡኻሪ 5971 ፣ ሙስሊም 2548)

ለወላጆች በጎ መዋል ቱሩፋት

ወላጆችን ማክበር ግዴታ ነው። እነሱን ማክበር ሽልማቱ ትልቅ ነው። እርዚቅ (ሲሳይ) ወይም በረካ ለማግኘት ሰበብ ነው። በዚህ አለም ህይወት መልካምነት ሲሆን በመጭው አለም ህይወት ደግሞ ጀነት ለመግባት ሰበብ ነው። ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ባፍንጫው አቧራ ውስጥ ይደፋ ፣ ባፍንጫው አቧራ ውስጥ ይደፋ ፣ ባፍንጫው አቧራ ውስጥ ይደፋ አሉ። የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! እሱ ማን ነው? ተብለው ተጠየቁ። እሳቸውም፡ በእርጅና እድሜ አንዳቸውን ወይም ሁለቱንም ወላጆቹን አግኝቶ ጀነት ያልገባ ሰው ነው አሉ።›› (ሙስሊም 2551)

ለወላጆቹ ደግ መሆን አሏህ በጣም የሚወደው ተግባር ነው። አብዱሏህ ቢን መስኡድ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በጣም የሚወደደው ተግባር ምንድነው? ብሎ ጠየቃቸው። እሳቸውም፡ በወቅቱ መስገድ ነው አሉ። እሱም ከዚያስ ምንድነው? አላቸው። እሳቸውም ወላጆችን ማክበር ነው አሉ። እሱም ከዚያስ? ምንድነው አላቸው። እሳቸውም ጅሃድ ፊ ሰቢሊላህ (በአሏህ መንገድ መታገል) ነው አሉት።›› (ቡኻሪ 527 ፣ ሙስሊም 85)

ወላጆችን ማክበር ከተጨማሪ ጅሃድ የበለጠ ነው። አንድ ሰው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መጣና ኡጃሂዱ (ልታገል ፣ ጅሃድ ላድርግ) አላቸው። እሳቸውም፡ ‹‹ወላጆች አሉህን?›› አሉት።እሱም አዎ አለ። እሳቸውም፡ ‹‹ለእነሱ ጥቅም ታገል›› አሉት።›› (ቡኻሪ 5972 ፣ ሙስሊም 2549)

ወላጆችን ማስከፋት

ወላጆችን አለማክበር ከትልልቅ ወንጀሎች ውስጥ አንዱ እና ከእነሱ ውስጥ ትልቁም ነው። በሐዲስ ውስጥ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡ ‹‹ከትልልቅ ወንጀሎች ሁሉትልቁ በአሏህ ላይ ማጋራት እና ወላጆችን አለማክበር ነው።›› (ቡኻሪ 6919 ፣ ሙስሊም 87)

ወላጆቻቸው በልጆቻቸው ላይ ያላቸው ግዴታዎች

١
1 በመልካም ነገር ያያዙትን እስከቻለው ድረስ መታዘዝ አለበት። ነገርግን ያዘዙት ነገር ሃጢያት ከሆነ በዚህ ላይ መታዘዝ የለበትም። ምክኒያቱም ፈጣሪውን አሏህን አምፆ ፍጡራኑን መታዘዝ ስለለ ነው።
٢
2 ልጃቸውን የሚጎዱ እና የሚበድሉ ቢሆኑ እንኳ ለእነሱ ደግ መሆን አለበት። ለአሏህ ባላንጣ (ተጋሪ) እንዲያበጅ ካላዘዙት በቀር፡፡ የጀሐነም እሳት ውስጥ ዘላለም ለመኖር ጥሪ ከማድረግ የበለጠ በልጃቸው ላይ ጉዳት ሚያደርሱበት በደል አለን? አሏህ እንዲህ አለ፡ "እውቀት በሌለህ ነገር በእኔ እንድትናገር ቢታገሉህ አትታተዘዛቸው። በቅርቢቱ አለም በመልካም ስራ ተወዳጃቸው።" (ሱረቱ ሉቅማን 15)
٣
3 እነሱን መንከባከብ እና በቻለው መንገድ ሁሉ እነሱን መታዘዝ ፣ መውደድ እና ማገልገል አለባችሁ። አሏህ እንዲህ አለ፡ "ጌታህ እሱን እንጅ ሌላን አትገዙ። ለወላጆቻችሁም መልካም ስሩ።" (ሱረቱ ኢስራዕ 23)
٤
4 እነሱን በማንኛውም መንገድ መጉዳት እና መበደል የለባችሁም። ‹‹ኡፍ›› ማለት ቢሆን እንኳ። በተለይ ደግሞ የእርጅና እድሜ ላይ በደረሱ ጊዜ። አሏህ እንዲህ አለ፡ "ጌታህ እንዲህ ሲል አዘዘ፡- እሱን እንጅ ሌላን አትገዙ። ለወላጆቻችሁም መልካም ስሩ። አንተ ዘንድ ሆነው የእርጅና እድሜ ላይ በደረሱ ጊዜ ኡፍ አትበላቸው።" (ሱረቱል ኢስራዕ 23)
٥
5 ለእነሱ ትሁት እና እራስን ዝቅ ማድረግ ያስፈልጋል። አሏህ እንዲህ አለ፡ "በእዝነት የመተናነስ ክንፍን ዝቅ አድርግላቸው። ‹‹ጌታየ ሆይ! በህፃንነቴ በርህራሄ እንዳሳደጉኝ እዘንላቸውም በል።" (ሱረቱል ኢስራዕ 24)
٦
6 ዘወትር ምስጋናን መግለፅ እና ለውለታቸው እውቅና መስጠት ያስፈልጋል። አሏህ እንዲህ አለ፡ "ሰውም ለወላጆቹ በጎ እንዲያደርግ በጥብቅ አዘዝነው። እናቱ ከድካም በላይ በሆነ ድካም ላይ ሆና ወለደችው። የጡት ማስጣያ ጊዜው ሁለት አመት እድሜ ነው። ለእኔም አመስግኑ። ለወላጆቻችሁም አመስግኑ። መመለሻችሁም ወደ እኔ ነው።" (ሱረቱ ሉቅማን 14)
٧
7 በደግነት ወጭያቸውን መሸፈን ያስፈልጋል። ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹አንተ እና ገንዘብህ ለአሏህ ተገቢዎች ናችሁ። ልጆችህ በላጭ ከሆኑ ከስቦችህ መካከል ናቸው። እናም ከልጆችህ ከስብ ብላ።›› (አቡዳውድ 3530)
٨
8 በህይወት እያሉ እና ከሞቱ በኋላ ለእነሱ ዱአ ማደረረግ ያስፈልጋል። የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹አንድ ሰው ሲሞት ስራዎቹ ይቋረጣሉ፤ ሶስት ነገሮች ሲቀሩ። ቀጣይነት ያለው ም ፅት ፣ ሰዎች የሚጠቀሙበት እውቀት እና (ለሞቱት) ዱአ የሚያደርግላቸው ልጅ ናቸው።›› (ሙስሊም 1631)
٩
9 ወላጆች ከሞቱ በኋላ ጓደኞቻቸውን እናወዳጆቻቸውን ማክበር ያስፈልጋ። የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹የመልካምነት ምርጡ ተግባር የአባቱን ወዳጆች (ጓደኞችን) በደግነት መንከባከቡ ነው።›› (ሙስሊም 2552)

ከወላጆች ጋር በሚኖራችሁ መስተጋብር ልትከተሏቸው የሚገቡ ስነ-ስርአቶች

١
1 በሚያወሩ ጊዜ ልብ ብሎ በጥሞና ማዳመጥ እና ስልክ እየነካኩ ትኩት አለመንፈግ።
٢
2 ከመጠየቃቸው በፊት የሚወዱትን ነገር ማድረግ ያስፈልጋል። የሚረብሻቸው እና የሚስጨንቃቸው ነገር ወደ እነሱ ከመምጣቱ በፊት መመለስ ግድ ነው።
٣
3 ለጥሪያቸው ምላሽ ለመስጠት ተቻኮል። ወደ እነሱ በመምጣትህ ደስታህን አሳያቸው።
٤
4 አሏህን ያለመታዘዝ ተግባር ሲፈፅሙ ባየህ ጊዜ የውዴታህን እና የጥበብ የተሞላበት ምክርህን ለግሳቸው።
٥
5 ወላጆችበደል በሚያደርሱብህ ጊዜ የደግነት ፣ የትዕግስት እና የአክብሮት መልስ ስጥ።
٦
6 ከእነሱ ተፃራሪ አቋም አትያዝ፤ ፈተናንም አታድርግባቸው።
٧
7 ፊታቸው ላይ ፈገግታ እንዲኖር አድርጉ።
٨
8 በግላዊ ጉዳያቸውም ቢሆን አማክራቸው። ሃሳብ አስተያየታቸውን አክብር።
٩
9 ከእነሱ ጋር አውራ ፣ ተጫወት ፣ የሚያስደስታቸው ከሆነ በእለት ተዕለት የኑሮ ጉዳይ ቢሆንም እንኳ ከእነሱ ጋር ተውያይ።
١٠
10 በጉዞ ምክኒያት ብትለያዩ ዘወትር ደውለህ አግኛቸው። ደህንነታቸውንም ጠይቅ።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር