መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የጁምዐህ ሶላት

የጁምአህ ሰላት በሙስሊሞች ላይ ግዴታ ከተደረጉ በጣም አስፈላጊ ሶላቶች አንዱ ነው። በዚህ ትምህርት ስለ ጁምአህ ሰላት ትሩፋት እና ፍርዶቹ ትማራለህ።

ስለ ጁምአህ ሰላት ትሩፋት ማወቅስለ ጁምአህ ሰላት አሰጋገድና ህጎቹ ማወቅ።   ከጁምአህ ሰላት ለመቅረት የምፈቀድላቸው ችግረኞችን መአወቅ።

የጁምዓ ሠላት

አላህ (ሱ.ወ) በጁምዓ ዕለት፣ በዙህር ሠላት ወቅት እጅግ በጣም የላቀ የኢስላም መገለጫና ከግዴታዎቹ ሁሉ የጠበቀ ሠላትን ደንግጓል፡፡ ይህ ሙስሊሞች በሳምንት አንዴ የሚሰባሰቡበት ዕለት ነው፡፡በዚሁ ዕለት የጁምዐው ኢማም የሚያቀርብላቸውን ምክርና ተግሳጽ ያዳምጣሉ ከዚያም የጁምዐን ሠላት ይሰግዳሉ፡፡

የጁምዓ ዕለት ትሩፋት

የጁምዓ ዕለት ከሳምንቱ ቀናቶች ትልቁና የላቀ ክብር ያለው ዕለት ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ከቀናቶች መካከል መርጦታል፡፡ ከተቀሩት ወቅቶች በበርካታ ልዩ ነገሮች አብልጦታል፡፡ ከነኚህም መካከል፡-

አላህ (ሱ.ወ)፡ ይህን ሕዝብ ከሌሎች ሕዝቦች ነጥሎ በዚህ ዕለት አልቆታል፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡ - ‹‹አላህ (ሱ.ወ) ከኛ በፊት ያሉትን የጁምዓን ዕለት አስቷቸዋል፡፡ ለአይሁዶች የቅዳሜን ዕለት፣ ለክርስቲያኖችም የእሁድን ዕለት አደረገላቸው፡፡ አላህ እኛን አመጣንና ለጁምዓ ዕለትም መራን፡፡›› ብለዋል፡፡ (ሙስሊም 856)

አደም የተፈጠረው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ የምፅዓት ዕለትም የምትከሰተው በጁምዓ ዕለት ነው፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡- #ፀሐይ ከምትወጣባቸው ቀናቶች በላጩ የጁምዐ ቀን ነው፡፡ኣደም የተፈጠረው በሱ ውስጥ ነው፡፡ ጀነት እንዲገባ የተደረገውም በሱ ውስጥ ነው፡፡ ከሷም እንዲወጣ የተደረገው በዚሁ ዕለት ውስጥ ነው፡፡ ሰዓቲቱም በጁምዓ ዕለት እንጂ አትከሰትም፡፡; ብለዋል፡፡ (ሙስሊም 854)

ጁምዓ ግዴታ የሚሆነው በማን ላይ ነው?

١
ወንድ፡ በሴት ላይ ግዴታ አይደለም
٢
ለአቅመ አዳም የደረሰ፡ በባሪያና ባልደረሰ ሕፃን ላይ ግዴታ አይደለም፡፡
٣
ነዋሪ፡ በመንገደኛ፣ እንዲሁም ከከተማና ከመንደር ርቆ በዱር በሚኖር ሰው ላይ ግዴታ አይደለችም፡፡

የጁምዓ ሠላት አፈፃፀምና ድንጋጌዎች

ለጁምዐህ ሶላት መዘጋጀት

ከጀሙዓ ሠላት በፊት ገላን መታጠብ፤ኹጥባ ከመጀመሩ ቀደም ብሎ በጊዜ ወደ መስጂድ መምጣትና ጥሩ ልብስ መልበስ የተወደደ ነው፡፡

የጁምዐህ ኹጥባ/ ዲስኩር

ሙስሊሞች ጁምዓ በሚሰገድበት ትልቅ መስጂድ ወይም መስጂድ ጃሚዕ ውስጥ ይሰባሰቡና፣ ኢማሙ በመድረክ ላይ በመውጣት ፊቱን ወደ ሰጋጆቹ በማዞር በሁለት ክፍል የተከፈለ ኹጥባ/ ዲስኩር ያደርግላቸዋል፡፡ በሁለቱ ኹጥባዎች መሐከል፣ ለመለያ ያክል ትንሽ ጊዜ በመቀመጥ እረፍት ያደርጋል፡፡ በኹጥባው ውስጥ፣ አላህን እንዲፈሩ ያስታውሳል፡፡ የቁርኣን አንቀጾችን እያጣቀሰ የተለያዩ ምክሮችና ተግሳጾችን ያስተላልፋል፡፡

ሰጋጆቹ ኹጥባውን በጥሞና ማዳመጥ አለባቸው፡፡ መነጋገር ወይም ከኹጥባው ተጠቃሚ እንዳይሆኑ በሚያደርጉ ነገሮች እራስን ማጥመድ ክልክል ነው፡፡ መስገጃ መነካካት ወይም አሸዋና አፈር እያነሱ መበተን እንኳን ክልክል ነው፡፡

ከዚህ ቀጥሎ፣ ኢማሙ ኹጥባውን ሲጨርስ ከመድረኩ ይወርዳል፡፡ ኢቃም ይደረግና በቁርኣን ንባቡ ድምፁን ከፍ በማድረግ ሁለት ረክዐዎችን ያሰግዳቸዋል፡፡

የጁምዓ ሠላት ያመለጠው ሰው

የጁምዓ ሠላት የተደነገገው የተወሰነ ያክል ሰው ለሚገኝበት ሁኔታ ነው፡፡ ስለዚህ፣ የጁምዓ ሠላት ያመለጠው ወይም በሆነ ምክንያት ከጁምዓ ሠላት የቀረ ሰው፣ በሱ ምትክ መስገድ ያለበት ዙህርን ነው፡፡ ብቻውን የሚሰግደው ጁምዓ ተቀባይነት የለውም፡፡

ከጁምዓ ሠላት የዘገየ ሰው

ከጁምዓ ሠላት የዘገየና ከኢማሙ ጋር ከረከዓ ያነሰውን ክፍል እንጂ ያልደረሰ ወይም ያላገኘ ሰው የሚሞላው ሠላት በዙህር መልክ ነው፡፡

ጁምዓ ግዴታ የማይሆንባቸው፣ ሴቶችና መንገደኛ የመሳሰሉት በሙሉ ከሙስሊሞች ጋር በመሆን ቢሰግዱ ሠላታቸው ተቀባይነት ያገኛል፡፡ በዚህም የዙህር ሰላት ግዴታ ይወርድለታል፡፡

የጁምዓ ሠላት ላይ የመገኘት ግዴታ

ኢስላማዊው ድንጋጌ፣ የጁምዓ ሠላት ላይ መገኘቱ ግዴታ በሆነባቸው ሰዎች ላይ ሁሉ በቦታው መጣድ ግዴታ መሆኑን አጥብቆ አሳስቧል፡፡ በዓለማዊ ጉዳይ ከርሱ መዘናጋትን አጥብቆ አስጥንቅቋል፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- #እናንተ ያመናችሁ ሆይ በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ መሸጥንም ተዉ፤ ይሃችሁ የምታውቁ ብትኾኑ ለናንተ በጣም የተሻለ ነው፡፡›› ይላል፡፡ (አል ጁምዓ 9)

ጁምዓን የተወ ሰው አላህ በምን አስጠነቀቀው?

ያለ ህጋዊ ምክንያት ከርሱ የሚቀርን ሰው በልቦናው ላይ መናፍቅነት መታተምን አስጥንቅቋል፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡ - ‹‹ያለ ምንም ምክንያት በመዘናጋት ሦስት ጁምዓን የተወ ሰው፣ አላህ (ሱ.ወ) በቀልቡ ላይ ያትምበታል፡፡›› ብለዋል፡፡ (አቡ ዳውድ 1052 አህመድ 15498) ‹‹በቀልቡ ላይ ያትምበታል›› ማለት ይጋርደዋል፣ ይሸፍነዋል፣ በውስጡ እንደ መናፍቃንና አመጸኞች ልብ መሃይምነትንና ድርቀትን ያበቅልበታል ማለት ነው፡፡

ከጁምዓ ለመቅረት የሚያስችል ምክንያት ምንድነው?

ከጁምዓ ለመቅረት የሚያስችል ምክንያት፡ ድንገተኛና ያልተለመደ፣ እጅግ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ወይም በኑሮ አለያም በጤና ላይ አስጊና አደገኛ ሁኔታ መከሰት ነው፡፡

በስራና ሃላፊነት ላይ ለመገኘት ሲባል ከጁምዓ መቅረት እንደ ህጋዊ ምክንያት ይታያልን?

በመሰረቱ፣ በስራና ሃላፊነት ላይ ለመገኘት ሲባል ከጁምዓ ሠላት መቅረት ህጋዊነት ወይም ተቀባይነት ያለው አይደለም፡፡ ከሁለት ሁኔታዎች በስተቀር

ከጁምዓ ሠላት ለመቅረት ህጋዊ ምክንያት ያለው ማን ነው?

1 እርሱ በቦታው ላይ በመኖሩና ከጁምዓ በመቅረቱ እንጂ ሊከሰት የማይችል ትልቅ ህዝባዊ ጥቅም ካለና ይህን ስራ እርሱ ከተወው ከፍተኛ ጉዳትና አደጋ የሚደርስ ከሆነ እርሱን ሊተካው የሚችል ማንም ከሌለ፡፡

ምሳሌ

١
• በድንገተኛ ክፍል የሚሰራ ዶክተር ድንገተኛ አደጋ የደረሰባቸው ቁስለኞችንና በሽተኞች የሚያክም ከሆነ
٢
• ዘበኛና ፖሊስ የሰዎች ንብረት በሌቦችና በወሮበሎች እንዳይዘረፍ በመጠብቅና በመከላከል ላይ ከተሰማሩ
٣
• በትላልቅ ኢንዳስትሪ ውስጥ የማሽኖችና መሳሪያዎችን ሂደት የሚከታተልና የሚቆጣር ቴክኒሻን ከሆነ ክትትል ለሴኮንዶች መቋረጥ የማይችል ከሆነ

ከጁምዓ ሠላት ለመቅረት ህጋዊ ምክንያት ያለው ማን ነው?

2 ስራው ብቸኛ የገቢ ምንጩ ከሆነ አስፈላጊ የዕለት ወጪዎቹን ምግቡን መጠጡንና ወሳኝ ጉዳዮችን ለራሱና ለቤተሰቦቹ የሚያስፈፅምበት ከዚያ ስራ ውጭ ምንም ከሌለው ሌላ ስራ እስከሚያገኝና ያለበት ችግር እስኪወገድለት ድረስ በዚያ ስራ ላይ በመቆየት ጁምዓ ሳይሰግድ ቢቀር ይፈቅድለታል፡፡ወይም ምግቡን መጠጡንና አስፈላጊ ጉዳዮችን ለራሱና ለቤተሰቦቹ የሚያስፈጽምበት እስከሚያገኝ ድረስ ይፈቀድለታል፡፡ ይሁን እንጂ ሌላ ስራና የገቢ ምንጭ ማስገኛ መንገድ የማፈላለግ ግዴታ አለበት፡፡

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር