መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት አራጣ (ወለድ)

በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ አራጣ ፅንሰ ሃሳብ እና ከእሱ ጋር ተያያዥ ስለሆኑ አንዳንድ የእስልምና ህግጋቶችን ትማራላችሁ።

1 ስለ ወለድ እና እሱን አስመልክቶ በእስልምና ህግ ውስጥ ያለውን ድንጋጌ ትማራላችሁ።2 የወለድ ክልከላን ጥበብ ታውቃላችሁ።3 አራጣ ወይም ወለድ በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ታውቃላችሁ።4 አራጣን በመተው እንዴት መቶበት እንደሚቻል ታውቃላችሁ።

ከሃያሉ አሏህ ጥበብ መካከል አራጣን በእስልምና ህግ ውስጥ ከትልልቅ ወንጀሎች ውስጥ አንዱ ማድረጉ ነው። ከእኛ በፊት በነበሩ ህዝቦች ላይም እርም ተደርጓል (ተከልክሏል)። ምክኒያቱም በማህበረሰቡ እና በአባላቶቹ ላይ ከፍተኛ ጥፋት እና ውድመትን ስለሚያስከትል ነው። አሏህ እንዲህ አለ፡ "(160) ከእነዚያ ይሁዳውያን በሆኑትም በተገኘው በደል ሰዎችንም ከአሏህ መንገድ በመካከላቸው በብዙ ምክኒያት ለእነሱ ተፈቅደው የነበሩትን ጣፋጭ ምግቦች በእነሱ ላይ እርም አደረግንባቸው። (161) ከእሱ በጥብቅ የተከለከሉ ሲሆኑ አራጣንም በመያዛቸውና የሰዎችን ገንዘብ ያለ አግባብ በመብላታቸው ምክኒያት እርም አደረግንባቸው (ከለከልናቸው)።" (ሱረቱ ኒሳእ 160-161)

የአራጣን አሳሳቢነት ከሚያሳዩት መካከል አራጣን በሚጠቀሙ ሰዎች ላይ ያደረሰው ዛቻ ነው። በእርግጥ አሏህ እንዲህ አለ፡ "(278) እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህን ፍሩ። ከአራጣም የተቀረውን ተው። አማኞች እንደሆናችሁ ተጠንቀቁ። (279) የታዘዛችሁትን ባትሰሩ ከአሏህ እና ከመልዕክተኛው በሆነች ጦር መወጋታችሁን እወቁ።" (ሱረቱል በቀራ 278-279) ሆኖም ሃያሉ አሏህ አራጣን (ወለድን) ከልክሏል፤ ባለቤቷንም በጦር ዝቶበታል።

ከዚህ በተጨማሪ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መከልከሉ ላይ ትልቅ አፅንኦት እና ከባድ ዛቻ ሰጥተዋል። ጃቢር (ረ.ዐ) እንዲህ አለ፡ ‹‹የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) አራጣ ተቀባዩን ፣ ከፋዩን ፣ መዝጋቢዋን እና ሁለቱን ምስክሮች ረግመዋል። እናም አሉ፡ ‹‹እነሱ ሁሉም እኩል ናቸው።›› (ሙስሊም 1598)

የአራጣ ትርጉም

በቋንቋ ደረጃ ወለድ ማለት መጨመር እና ማሳደግ ነው። አሏህ እንዲህ አለ፡ "አንዲቱ ህዝብ ከሌላይቱ ህዝብ የበዛች ለመሆኗ" (ሱረቱ ነህል 92) ያ ማለት በቁጥር ይበልጣል ማለት ነው።

የወለድ ትርጉም

ሸሪኣዊ ትርጉሙ መገበያያ ነገሮችን በማበላለጥ ወይም ብድርን ከትርፍ ጋር መክፈል ስሆ በሸሪኣህ ተከልክሏል

የአራጣ አይነቶች

١
ሪባ አል-ፈድል (የማበላለጥ አራጣ)
٢
የብድር አራጣ

ሪባ አል-ፈድል (የማበላለጥ አራጣ)

ገደብ እንደተደረገባቸው የተጠቀሱ የሸቀጥ ምድቦች ላይ ተጨማሪ መጠን ማድረግ ነው። ጭማሪው ያለው ተመሳሳይ በሆነ ነገር ላይ የአራጣን ገንዘብ በአራጣ ገንዘብ መለዋወጡ ላይ ነው። ልክ 1 ኪሎ ጥሩ የተምር በ2 ኪሎ መጥፎ የተምር እንደ መሸጥ ማለት ነው።

የብድር አራጣ

ሸቀጦች መድረስ ካለባቸው ቦታ እንዳይደርሱ አቅርቦቱን ማዘግየትን ይይዛል። ሁለት ሸቀጦችን ለአራጣ ሲባል ላትርፍ ሽያጩን ማዘግየት ነው። መቀበልን በማዘግየት ልክ የስንዴ ሰአአ (መለኪያ) በገብስ መለኪያ እንደመቀያየር ማለት ነው።

የአራጣ ብያኔ

አራጣ በቁርአን ፣ በሱና እና በኡለማኦች ስምምነት መሰረት የተከለከለ ነው። አነዋዊ (ረሂመሁሏህ) እንዲህ አለ፡ ‹‹ሙስሊሞች የአራጣን ክልከላ እና ትልቅ ሃጢያቶች ውስጥ አንዱ መሆኑን በማያሻማ መልኩ ይቀበላሉ፤ ያረጋግጣሉ።›› (አል-መጅሙእ 9/391)

የአራጣ ክልከላ ጥበብ

1 ትክክለኛ የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴን ያበረታታል። አራጣ የሚበላ ሰው ገንዘቡን እራሱን ወይም ማህበረሰቡን በሚጠቅም ስራ ላይ አያውለውም። ለምሳሌ ግብርና ፣ ኢንዱስትሪ ፣ ንግድ ወይም ሌላ የሥራ መስክ

2 ያለ ሃሳብ ገቢ ማግኘትን ይከለክላል፡ እስልምና ሁለት ወገኖች ጥቅም በሚያገኙበት መልኩ የገነዘብ ለውውውጥን ይቆጣጠራል። ሁለቱም የሆነ ነገር አስተዋፅኦ ማድረግ እና በመልሱ የሆነ መገር መውሰድ አለባቸው። ይህ ደግሞ በአራጣ ውስጥ የለም።

3 አራጣ በሰዎች መካከል ያለውን መልካም ነገር የሚያጠፋ ነው። ይህ ደግሞ ውለታን ፣ በመካከላቸው በጎ ስራን እና ቅንነት በማስፋፋት ውስጥ የእስልምና አላማ ጋር የሚቃረን ነው።

4 ብዝበዛን ይከላከላል፡ አበዳሪው ብዙ ጊዜ አራጣን በመጫን የተበዳሪውን ፍላጎት ደህና አድርጎ ይበዘብዛል።

5 ኢፍትሃዊነትን ያስቀራል፡ አራጣ አንደኛው ወገን የሚቸገርበት እና የሚበዘብዝበት ኢፍትሃዊነት ነው። አሏህ ሁሉንም የኢፍትሃዊነት (የበደል) አይነቶች ከልክሏል።

አራጣ የሚያደርሰው ጉዳት

የአራጣ ጉዳቶች እና አደጋዎች ግዙፍ ናቸው። ይህ ጉዳት እና አደጋ ከግለሰቦች ህይወት እስከ አጠቃላይ ማህበረሰቡ ድረስ በሁሉም ዘርፍ የተለጠጠ ነው።

1 የግብረገብ እና መንፈሳዊ ጉዳት

አራጣ ባለቤቱ ላይ ስግብግብነትን ፣ የልብ መድረቅን እና የሃብት ባርነትን ያስከትልበታል። ምክኒያቱም በሌሎች ላይ ፍላጎቶቻቸውን ፣ ድክቶቻቸውን እና ድህነታቸውን ተጠቅሞ መበዝበዝን እና መበደልን ያመጣልና ነው።

2 ማህበራዊ ቀውስ

አራጣ ማህበረሰቦችን ከሚያጠፉ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነው። አንድን ማህበረሰቦችን የተፈረካከሱ እና የተበታተኑ ያደርጋቸዋል። በእሱ ውስጥ ጠንካራው ደካማውን ያደቀዋል። አንድም ሰው ጎረቤቱን አይረዳም፤ ይህን በማድረጉ ጥቅም የሚያገኝበት ካልሆነ በቀር።

3 የኢኮኖሚ (የምጣኔ ሃብት) ጉዳት

አራጣ በሁሉም ደረጃዎች በምጣኔ ሃብት ስርአት ላይ መታወክን እና መቃወስን ያደርሳል። በግለሰቦች ላይ እዳ እንዲከማች ያደርጋል። የማህበረሰቡ ፍሬያማ እና ትክክለኛ ምርት ይቀንሳል ወይም ይቆማል።

ከአራጣ ለመቶበት ሊሟሉ የሚገባቸው ቅድመሁኔታዎች

١
1 የአራጣ ግብይቶችን ሁሉ ማቋረጥ
٢
2 ባለፉ የአራጣ ግብይቶች ሁሉ መፀፀት
٣
3 ይሀን ሃጢያት ደግሞ ላለመፈፀም ቁርጥ አድርጎ መወሰን እና መተው
٤
4 ከተቻለ የተገኘውን ትርፍ ሳያጓድሉ ለባለቤቱ መመለስ ይህ ካልሆነ ደግሞ ትርፉን ለድሆች እና ለተቸገሩ ሰዎች እርዳታ መስጠጥ ያስፈልጋል።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር