መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት ተቀማጭ (አደራ)

በዚህ ትምህርት ውስጥ በእስልምና ህግ ውስጥ የተቀማጭ ገንዘብ ሃሳብን እና ከእሱ ጋር ተያያዥ ስለሆኑ የህግ ውሳኔዎች ትማራላችሁ።

1 ስለ ተቀማጭ  እና ከሱ ጀርባ ያለውን ጥበብ ትማራላችሁ።2 ከተቀማጭ  ጋር የተያያዙ የሸሪዐህ ብያኔዎችን ታውቃላችሁ።

የተቀማጭ ፅንሰ ሃሳብ

ያለ ምንም ክፍያ እንድጠብቁለት ሌሎች ሰዎች ዘንድ ንብረት ማስቀመጥ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው ሰአት ፣ መኪና ወይም ገንዘብን የሆነ ሰው ዘንድ በአደራ መልክ እንዲቀመጥለት ማድረግ ነው።

የአዳራ ተቀማጭ ብያኔ

የአደራ ተቀማጭ የተፈቀደ ውል ነው። ሁለቱ የተዋዋሉ ሰዎች በፈለጉ ጊዜ ውሉን ሊያቋርጡ ይችላሉ። ባለቤቱ ከጠየቀ ለእሱ ሊመልስለት ይገባል። አደራ የተሰጠው ሰው ከመለሰለት ባሌቱ መቀበል አለበት። ይህም በጎነት እና በደግነት ተግባር መተባበር ነው።

የተቀማጭ ንብረት ህጋዊነት ጥበብ

አንድ ሰው ንብረቱን የሚያስቀምጥበት ተገቢ ቦታ ባለማግኘቱ ፣ በህመም ምክኒያት ባለመቻሉ ፣ እሰረቃለሁ ብሎ በመፍራት ሊቸገር ይችላል።ግ ን የሆነ ሰውበአደራ መልክ እንዲያስቀምጥለት ልመቸው ይችላል።

ለዚህም ነው አሏህ ንብረት ማስቀመጥን የፈቀደው። በአንድ በኩል ንብረቱን ሚጠበቅብበት እና በሌላ በኩል ደግሞ ያስቀመጠለት ሰው ምንዳ ሚያገኝበት ነው። ይህ በሰዋች ላይ ያቀላል፤ ሰዎች ፍላጎቶቻቸውን እንዲያሟሉ ይረዳል።

ንብረትን ማስቀመጥ በቁርአን ፣ በሱና እና በኡለማኦች ስምምነት መሰረት እና በቂያስ የተፈቀደ ነው። አሏህ እንዲህ አለ፡ "በእርግጥ አሏህ አደራዎችን ወደ ባለቤተቻቸው እንድትመልሱ ያዛችኋል።" (ሱረቱ ኒሳዕ 58)

አቡ ኹረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡ ‹‹አደራ ለሰጣችሁ ተቀማጩን (አደራውን) መልሱለት። የከዳችሁንም ሰው አትክዱ።›› (አቡዳውድ 3535)

ተቀማጭ ንብረት የመቀበል ሁክም (ውሳኔ)

የሆነ ሰው ገንዘብ ሊያስቀምጥልኝ ይችላል ብሎ እምነት የተጣለበት ሰው ገንዘቡን መቀበል የተወደደ ነው። ምክኒያቱም ይህ በመልካምነት እና በደግነት በጋራ መረዳዳት ነውና። እንዲሁም ጠብቆ በማቆየቱ ከአሏህ ምንዳ (ሽልማት) የሚያገኝበት ነውና።

የተቀማጭ ገንዘብ ምሰሶዎች

١
1 አስቀማጩ፡ የተቀማጩ ገንዘብ ባለቤት ነው።
٢
2 አደራ ተቀባዩ፡ ተቀማጩን ገንዘብ ተቀብሎ ጠብቆ የሚያኖርለት ሰው ነው።
٣
3 ተቀማጩ ገንዘብ፡ በአደራ መልክ የተሰጠው ገንዘብ ወይም ንብረት ነው።
٤
4 የውል ቅፅ፡ ሁለቱ ሰጭ እና ተቀባይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ቅፅ ነው።

አደራ ተቀባዩ የተቀማጭ ገንዘቡ ተጠያቂ የሚሆንበት ሁኔታ

١
1 ተቀማጭ ገንዘቡን በመጠበቅ ቸል ማለት
٢
2 ያለ በቂ ምክኒት እና ያለ አደራ ሰጭው ፈቃድ ከሌላ ሰው ዘንድ ማስቀመጥ
٣
3 ተቀማጩን ገንዘብ መጠቀም

ተቀማጭ ገንዘቡ ከአደራነት ወደ ዋስትና የሚለወጥበት ሁኔታዎች

١
1 ተቀማጭ ገንዘቡ ወይም እቃ ከሌላ እቃ ጋር በሚደባለቅበት ጊዜ እና መለየት በሚያስቸግርበት ጊዜ
٢
2 ተቀማጩ ገንዘብ የተቀመጠበት መንገድ ህግን የተላለፈ እና (ለዝርፊያ ወይም ለጉዳት የሚዳርገው) ሲሆን
٣
3 ተቀማጩን ገንዘብ ወይም ንብረት ተመሳሳይ ከሆነ ተቀማጭ የሚደረገውን ጥበቃ አለመድረግ

ተቀማጭ ገንዘቡ በአስቀማጩ ሰው ከጠፋ ወይም ከተበላሸ እና የጠፋው እና የተበላሸው ድንበር አልፎበት ወይም ችላ በማለቱ እስካልሆነ በቀር ዋስትና የለበትም። ነገርግን ተቀማጩን ገንዘብ ደህንነቱ በሚጠበቅበት ከእሱ ጋር አቻ በሆነ መልኩ ከልሎ ማስቀመጥ አለበት።

አደራውን ተቀብሎ ያስቀመጠው ሰው የሆነ ነገር ካስፈራው እና ጉዞ ኖሮት መጓዝ ቢፈልግ፤ ተቀማጭ ገንዘቡን ለባለቤቱ ወይም ለወኪሉ መመለስ አለበት። ይህን ማድረግ ካልተቻለ ታማኝ ለሆና ባለስልጣን በአደራ መልክ መስጠት አለበት። ይህም ሊሆን ካልቻለ ለባለቤቱ ይመልስ ዘንድ በጥብቅ ለሚያምነው ሰው በአደራ መልክ መስጠት አለበት።

አንድ ንብረት ወይም እቃ በአደራ መልክ ተሰጥቶት ከእሱ ጥበቃ ውጭ ያደረገ ፣ መለየት ከማይችለው ከሌላ እቃ ጋር ያደባለቀ ሰው የእቃው አይነት ቢጠፋ ወይም ቢበላሽ ማካካስ አለበት።

አደራ ተቀባዩ ሰው ታማኝ ሆኖ ሳለ አደራ በተሰጠበት ድንበር አልፎ ወይም ችላ ብሎ ካልሆነ በቀር ዋስትና የለበትም። ተቀማጭ ገንዘቡን መመለሱን ወይም ለመጥፋቱ እና ለመበላሸቱ እሱ ተጠያቂ ስለመሆኑ እና የቸልተኝነት ጥፋት የነበረበት ስለመሆኑ ማስረጃ ከሌለ የእሱን ቃል ከመሃላው ጋር መቀበል እና ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ በቂ ነው።

ተቀማጩን ገንዘብ ከመመለስ ጋር የተያያዙ የህግ ውሳኔ (ሁክም)

ተቀማጩ ገንዘብ አደራ ነው። ባለቤቱ እንዲመልስለት በጠየቀ ጊዜ አደራ ተቀባዩ መመለስ አለበት። አደራ ሰጩ እንዲመልስለት ሲጠይቀው ካልመለሰለት እና ለመጥፋቱ ወይም ለመበላሸቱ በቂ ምክኒያት ከሌለው ማካካስ አለበት። አሏህ እንዲህ አለ፡ "በእርግጥ! አደራዎችን ወደ ባለቤቶቻቸው እንድትመልሱ ያዛችኋል።" (ሱረቱ ኒሳዕ 58)

የተቀማጩ ገንዘብ ባለቤቶች ከአንድ ሰው በላይ ሆነው ሳለ ከእነሱ መካከል አንዱ ድርሻው እንዲሰጠው ሲጠይቅ፤ ገንዘቡ የሚለካ ፣ የሚመዘን ወይም የሚቆጠር ከሆነ ድርሻው ይመለስለታል።

የተቀማጭ ገንዘብ ውል የሚያበቃበት ሁኔታ

١
1 ተቀማጩን ገንዘብ ማስመለስ ወይም መመለስ
٢
2 የተቀማጩ ገንዘብ ባለቤትነት በሽያጭ ወይም በስጦታ መልክ ለሶስተኛ ወገን ሲተላለፍ
٣
3 ከአደራ ሰጩ ወይም ከተቀባዩ ሀላፊነት ስነሳ
٤
4 ከአደራ ሰጩ ወይም ከተቀባዩ አንዱ በሞተ ጊዜ

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር