መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የሴቶች መብት በእስላም

በዚህ ትምህርት ውስጥ ሴት ልጅ በእስልምና ያላትን መብቶች ትማራላችሁ

1 ሴቶች በእስልምና ያላቸውን ክብር እና ቀደምት ህዝቦች ለሴት ልጅ የነበራቸውን መጥፎ አመለካከት መካከል ያለውን ልዩነት ታውቃላችሁ።2 እስልምና በፆታ እክልነት ዙሪያ ያለውን ህግጋት ታውቃላችሁ3 የእስልምና ህግ በተለያዩ ዘርፎች ለሴቶች የሰጠውን መብት ታውቃላችሁ

እስልምና ለሴቶች ያለው እንክብካቤ

የእስልምና ሃይማኖት በመለኮታዊ አስተምህሮቶቹ እና ጥበባዊ በሆነው መመሪያው ሙስሊም ሴትን ይንከባከባል ፣ ክብሯን ይጠብቃል ፣ ልቅናዋን እና ደስታዋን አረጋግጦላታል ፣ ከጥርጣሬ ፣ ከፈተና እና ከክፉ ነገር ሁሉ አርቆ ምቹ እና የተደላደለ ህይወትን አዘጋጅቶላታል። ይህ እንክብካቤ ብዙ መልክ እና ቅርፅ አለው።

የሴት ልጅ ክብር እና ከፍ ያለ ደረጃ

እስልምና ለሴቶች ሰብአዊነትን እና ክብርን እና የትም ቢሆኑ እንኳ የላቀ ደረጃን ሰጥቷቸዋል። ሴት ልጅ እናት ፣ ሚስት ፣ ሴት ልጅ ናት። ሆኖም ለእሷ ማዘን ፣ ደግ መሆንን እና ልዩ አትኩሮት መስጠት አዟል። በአንፃሩ የሴቶችን ሚና የሚቀንሱ ፣ የሚያዋርዱ እና የሚያንኳስሱ የተዛቡ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ፣ እና ማህበራዊ ትውፊቶችን ይዋጋል።

ኡመር ኢብን ኸጧብ (ረ.ዐ) እንዲህ አለ፡ ‹‹በአሏህ ይሁንብኝ በጃሂልያ ውስጥ ሴቶችን እንደ ጉዳይ አንቆጥራቸውም ነበር። አሏህ የገለጠውን ነገር እስኪገልጥ ድረስ እና የሰጠውንም እስኪሰጥ ድረስ።›› (ቡኻሪ 4913 ፣ ሙስሊም 1479) የእስልምና ብርሃን ብቅ ያለው ከ1400 አመት በፊት ነው። ሆኖም የሴትን ልጅ ደረጃ ከፍ አድርጓል። በእነሱ ላይ የተቃጣን በደል ሁሉ ሽሯል። ከእነዚህ በደሎች እና ኢፍትሃዊነት መካካል የንብረት ባለቤት የመሆን እና ውርስ መውረስ ይከለከሉ ነበር። ሚስት ባሏ ከሞተ በኋላ ትወረስ ነበር። እንዲሁም ከአስክሬኑ ጋር አብራ እንድትቃጠል እና እንድትቀበር ይደረግ ነበር። ከዚህ በተጨማሪ ትሸጥ ትለወጥ ነበር። ይህ ተግባር እስከ ሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ድረስ በእንግሊዝ ውስጥ መተግበሩን ቀጥሎ ነበር።

የወንዶች እና የሴቶች እኩልነት

እስልምና የአለማት ጌታ ፣ ሁሉን ሰሚ ፣ ፍትሃዊ ፣ ጥበበኛ የሆነው አሏህ ሃይማኖት ነው። ከአሏህ ፍትህ እና ጥበብ ውስጥ በሚለያዩበት ጉዳይ እኩል አያደርግም። በሚመሳሰሉበት እና አንድ በሚሆኑበት ጉዳይ ደግሞ በመካከላቸው ልዩነት አያደርግም። በእስልምና ህግ ወንዶች እና ሴቶች እኩል የሚሆኑት አንድ በሚሆኑበት እና በሚያመሳስላቸው ነገር ነው። በተለያዩበት ነገር ደግሞ በመካከላቸው ልዩነትን ያደርጋል። እንደየ ችሎታቸው እና እንደየ ፍላጎቶቻቸው መብትን እና ግዴታዎችን አድርጓል። እስልምና ለሴቶች በሁሉም ዘርፎች የሚገባቸውን ደረጃ እና ቦታ ሰጥቷቸዋል። በብዙ ዘርፎችም ከወንዶች ጋር እኩል አድርጓቸዋል። ከነዚህም፦

በመሰረታዊ አፈጣጣር

ቀደምት ህዝቦች ለሴቶች የነበራቸው ንቀት ሴቶችን ከሰውነት ደረጃ የሚያስወጣቸው ፅንፍ የያዘ ነበር። አርስቶትል እንዲህ ይላል፡ ‹‹ሴት ልጅ ያልተሟላች ጎደሎ ፍጡር ናት። ተፈጥሮም ከፍጥረቶች ሁሉ ዝቅ ያለ ቦታ ላይ አስቀምጣታለች።›› ሶቅራጥስ ደግሞ ከተመረዘ ዛፍ ጋር ያነፃፅራታል። በአንድ ወቅት ሮም ውስጥ በተካሄደው ታላቅ ጉባኤ ሴት ልጅ ነፍስም ሆነ ዘላላማዊነት የሌላት እና ከዚህ አለም ህይወት ባሻገር የማትኖር እርኩስ ናት። ስጋ አትበላም ፣ አትስቅም ፣ አታወራም የሚል ማደማደሚያ አስቀምጠው ነበር። ፈረንሳዮች ደግሞ በ586 አመት ውስጥ ስብሰባ ሲያካሂዱ ‹‹ሴት ልጅ ሰው ናት አይደለችም? ነፍስ አላት የላትም?›› በሚል ሃሳብ ዙሪያ ተወያይተው ሰው ከሆነች ከወንድ ልጅ ጋር እኩል ደረጃ አላት ልንል ነው የሚል ሙግት ገጥመው በመጨረሻ የሰው ልጅ ናት ነገርግን ወንድን ለማገልገል የተፈጠረች ናት የሚል ማደማደሚያ ላይ ደረሱ። በተቃራኒው እስልምና ሁለቱም ፆታዎች በአፈጣጠራቸው እኩል መሆናቸውን ያረጋግጣል። አሏህ እንዲህ አለ፡ "እናንተ ሰዎች ሆይ! ያነን ከአንዲት ነፍስ (ከአደም) የፈጠራችሁን ከእርሷም መቀናጆዋን (ሐዋን) የፈጠረው ከእነሱ ብዙ ወንዶችን እና ሴቶች የበተነውን ጌታችሁን ፍሩ። ያነንም በእሱ የምትጠየቁበትን አሏህን እና ዝምድናዎችንም (ከመቁረጥ) ተጠንቀቁ። አሏህ በእናንተ ላይ ተጠባባቂ ነውና።" (ሱረቱ ኒሳዕ 1)

ሃይማኖታዊ እኩልነት

እስልምና ወንዶች እና ሴቶችን በሃይማኖታዊ ተግባራት እና ግዴታዎች ፣ በሽልማታቸው እና በቅጣታቸው በዚህ አለም እና በመጭው አለም ህይወት እኩል አድርጓቸዋል። አሏህ እንዲህ አለ፡ "ከወንድ ወይም ከሴት አማኝ ሆኖ በጎ የሰራን መልካም ኑሮን በእርግጥ እናኖረዋለን። ይሰሩትም ከነበሩት ነገር በመልካም ምንዳቸውን እንመነዳቸዋለን።" (ሱረቱ ነህል 97) ሃያሉ አሏህ እንዲህ አለ፡ "ከወንድ ወይም ከሴት እሱ አማኝ ሆኖ ከበጎ ስራዎች አንዳችን የሚሰራም ሰው እነዚያ ገነትን ይገባሉ። በተምር ፍሬ ላይ ያለችን ነጥብ እንኳ አይበደሉም።" (ሱረቱ ኒሳዕ 124) በአንድ ወቅት ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በህልሙ ግኑኝነት ያደረገ መሆኑን ሳያስታውስ ረጥቦ ስለ ተነሳ ሰው ተጠይቀው ሲመልሱ እንዲህ አሉ፡ ‹‹መታጠብ ይገባውል አሉ።›› በህልሙ ግኑኝነት ሲያደርግ አይቶ ነገርግን ምንም አይነት ምልክት ስላላገኘ ሰው ተጠይቀው ሲመልሱ ደግሞ እንዲህ አሉ፡ ‹‹መታጠብ አይጠበቅበትም አሉ።›› ኡሙ ሱለይም ‹‹ሴት ያን ካየችስ ገላዋን ትታጠባለችን?›› አለች። እሳቸውም ‹‹አዎ! ሴቶች የወንዶች እህቶች ናቸው›› አሉ።›› (አቡዳውድ 236)

በአሏህ መልዕክተኛ መልዕክት ያመነችው የመጀመሪያዋ ሴት ነበረች። እሷም የሙዕሚኖች እናት የሆነችው ኸድጃ (ረ.ዐ) ናት። ሴቶች ወደ ሀበሻ የተደረገውን የመጀመሪያ ስደት ተጋርቷል፤ ከየስሪብ መቶ ነቢይን ቃልክዳን የገባ ልኡካን ቡድንም ተጋርቷል

በእስልምና ታሪክ ውስጥ ሴቶች ደማቅ እና አንፀባራቂ ምሳሌን ፅፈው አልፈዋል። በመልካም ባህሪያቶቻቸው ፣ ጥልቅ በሆነ እውቀታቸው እና የእስልምናን መልዕክት በመረዳት አቅማቸው በደንብ ይታወቃሉ። በተለያዩ ዘርፎች ፣ በሃይማኖታቸው ፣ በሳይንስ እና በትምህርት የላቁ ስመጥሮች ነበሩ። ከእነሱ መካከል ደግሞ በጣም የምትታወቀው የምዕመናን እናት የሆነቸው አኢሻ (ረ.ዐ) ናት።

ሴቶች ልክ እንደ ሐጅ እና ኡምራ ሁሉ ግዴታ ፣ የተወደደ እና የተፈቀደ በሚለው ሁክም መሰረት በህብረት ሶላት ፣ የዝናብ ልመና ሶላት ፣ በሁለቱ ኢዶች በጀመአ (ህብረት) ሶላት ፣ በጁምአ ሶላት ከወንዶች ጋር አብረው ይሳተፋሉ። ከዚህ በተጨማሪ ወደ እስልምና ጥሪ እንዲያደርጉ ፣ በመልካም እንዲያዙ እና ከመጥፎ ነገር ሁሉ እንዲከለክሉ ታዘዋል። ብዙ ሃይማኖታዊ ተግባራትን እንዲፈፅሙ ታዘዋል። ይህ የሚያመለክተው ሁለቱም ፆታዎች በሃይማኖት ጉዳይ እኩል መሆናቸውን ነው። ብቸኛው ልዩነታቸው በእነሱ መካከል ያለው አካላዊ ጾታዊ አፈጣጠር ጋር የተያያዘ ልዩነት ብቻ ነው።

የእኩልነት መርህ በሃይማኖታዊ ተግባራት ውስጥ ሁለቱ ፆታዎች እንደጥቅል በተቀመጡ በተፈጥሮ ያላቸውን ልዩነትም ከግምት ውስጥ ያስገባል። ከዚህ የሚገኘው ውጤት በተልዕኮዎቻቸው መለያየት ነው። እያንዳንዱን ግለሰብ በትክክለኛው እና በሚገባው ቦታ ላይ ያስቀምጣል። ይህ ደግሞ በህይወት ውስጥ ውህደትን ይፈጥራል። ወንድ የሴትን እና የልጆችን ወጭ የመሸፈን ግዴታ አለበት። እነሱን መጠበቅ እና ቤተሰቡን መንከባከብ አለበት። ሴት ደግሞ በቤቷ ፣ በባሏ እና በልጆቿ ላይ ሃላፊነት አለባት። ልትወጣው የሚገባ የራሷ የሆነ ሃላፊነት አለባት።

እስልምና ከ1400 አመታት በፊት መልዕክቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ለሴቶች የተረጋገጡትን የዜጎች ፣ የማህበራዊ እና የግል መብቶቻቸውን ሰጥቷቸዋል፡፡ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በዚህ ዘመን ለሴቶች መብት ጥብቅና ከመቆማቸው በፊት እስልምና ለሴቶች ዋስትና ሰጥቷል።

የሴቶች የሲቪል እና የማህበራዊ መብቶች

١
የሴቶች የመማር እና የማስተማር መብት፡ በእርግጥ እስልምና ሳይንሳዊ እውቀት መሻት ያበረታታል። ይህ ደግሞ ለወንዶችም ለሴቶችም ነው።
٢
የሴቶች የመስራት መብት፡ በመሰረቱ መስራት ያለበት እና ወጭን መሸፈን ያለበት ወንድ ነው። ነገርግን ሴት ልጅ መስራት ከፈለገች በእስልምና ውስጥ የሚከለክላት ምንም ነገር የለም። መስራት ያለባት ግን በእስልምና አስተምህሮት ፣ ደንቦች እና ህግጋት መሰረት ነው።
٣
የሴቶች የመውረስ መብት፡ የአሏህ መጽሐፍ ፣ የነብዩ ሱና እና የፉቅሃዎች መጽሐፍት በእንደዚህ አይነት ጉዳዮች አቅፈው የያዙ ናቸው። ሴቶችም ተመሳሳይ የውርስ ድርሻ ያገኛሉ።
٤
የሴቶች የንብረት ባለቤት የመሆን መብት፡ ሴቶች ስራ በመስራት ወይም ውርስ በማግኘት የንብረት ባለቤት የመሆን ሙሉ መብት አላቸው። ንብረቷን እንደፈለገች የማድረግ ሙሉ ነፃነትም አላት። በገንዘቧ ላይ አንድም ተቆጣጣሪ የለባትም፤ አባቷ ፣ ባሏ ወይም ሌላ ሰው ቢሆንም እንኳ።

የሴት ልጅ መብቶች በግል እና በትዳር ጉዳይ ውስጥ

١
1 ጥሩ (መልካም) ባል የመምረጥ ፣ የመቀበል እና ያለመቀበል መብት
٢
2 ጥሎሽ የማግኘት መብት
٣
3 የንብረት እገዛ የመግኘት ፣ ለእርሷ እና ለልጆቿ አስፈላጊ ወጭዎች የመሸፈንት መብት
٤
4 ከባሏ ጋር የተከበረ ህይወት የመኖር እና በመልካም ቃል እና ተግባር የመተዳደር መብት
٥
5 ባል ሌሎች ሚስቶች በሚኖሩት ጊዜ እኩል አያያዝ እና እንክብካቤ የማግኘት መብት
٦
6 ንብረት የማፍራት ነፃነት እና ከባሏ ውጭ በራሷ ለንብረቶቿ ዋስትና የመሆን መብት
٧
7 ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ እና መለያያት አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ በገንዘብ ረስን የማስፈታት፤ ፍች የመጠየቅ እና ፍች የማግኘት መብት
٨
8 እንደገና ካላገባች ልጆቿን የማሳደግ እና ሞግዚት የመሆን መብት

ከላይ የተጠቀሱት ሴቶች በእስልምና ውስጥ ያላቸውን መብት የሚያንፀባርቁ ምሳሌዎች ናቸው። ከዚህ ባሻገር እስልምና ለሴቶች ያጎናፀፋቸው መብቶች በጣም በርካታ ናቸው።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር