መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የላኢላሀ ኢለላሀ ምስክርነት ቃል

እስልምና ሁለቱን ምስክርነቶች "ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ እናም መሐመድ የአላህ መልእክተኛ መሆናቸውን እመሰክራለሁ" የምለውን ቃል ከሁሉ የላቀና የተከበረ አደረገው። በዚህ ትምህርት፣ “ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም” ለሚለው ምስክርነት ትርጉም፣ ደረጃ እና ምሰሶዎች ትማራለህ።

  • ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ የምስክርነትን ትርጉም ማወቅ
  • ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም የሚለውን የምስክርነት ደረጃ ማወቅ
  • ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ የምስክርነትን ምሰሶዎች ማወቅ

እስልምና ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም የሚለውን የተውሂድ ቃል ትልቅና የተከበረ ደረጃን ይሰጣል።

የላኢላሀ ኢለላህ ቃል ደረጃ

١
በሙስሊም ላይ የመጀመሪያው ግዴታ ይህን ቃል ማረጋገጥ ነው፡፡ አንድ ሰው ወደ እስልምና መግባት ከፈለገ በቃሉ ውስጥ ባለው ፅንሰ-ሃሳብ ማመንና ቃሉን መናገር ይኖርበታል፡፡
٢
ቃሉ ባካተተው ዕውነታ ከልቡ አምኖና የአላህን ውዴታ ፈልጎ ቃሉን በንግግር በመግለፅ የመሰከረ ሰው ከእሳት ቅጣት ነፃ ለመውጣት ሰበብ ይሆነዋል፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ ብለዋል… “(የአላህን ውዴታ በመፈለግ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ብሎ የመሰከረ ሰው አላህ በርሱ ላይ እሳትን እርም አድርጓታል፡፡” (አል-ቡከሪ፡415)
٣
ይህ ቃል በውስጡ ባካተተው ፅንሰ-ሃሳብ አምኖ የሞተ ሰው የጀነት ነዋሪ ይሆናል፡፡ ነቡዩ (ሰ.ዐ.ወ.) እነዲህ ብለዋል … “ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን አውቆ የሞተ ሰው ጀነት ገብቷል፡፡”(አህመድ፡464)

•ይህ በመሆኑም ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን ማወቀና መመስከር የግዴታዎች ሁሉ ተላቁ ግዴታ ነው፡፡

“ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” የሚለው ቃል ትርጉም

ይህ ማለት ብቸኛ ከሆነው አላህ በስተቀር በዕውነት የሚመለከ አምላክ የለም ማለት ነው፡፡ ከተቀደሰውና ከፍ ካለው አላህ በስተቀር ከማንም ላይ መለኮታዊነትን መሻር ማለት ሲሆን መለኮታዊ ስልጣንን አንድና አጋርለሌለው አላህ ብቻ ማረጋገጥ ማለት ነው፡፡

«አል-ኢላህ» (አምላክ)! ማለት የሚመለክ ማለትነው፡፡ ቀልቦች በመተናነስ በማክበር በመማጸን፤በመፍራት፣ በርሱ ላይ በመመካት ያመልኩታል፡፡ አንድን ነገር ያመለከ ሰው የተናነሰ፤ የወደደ፤ የከጀለ፤ ያንን ነገር ከአላህ ሌላአምላክ አድርጎ ይዞታል፡፡ ከተቀደሰው፣ ከፍ ካለውናፈጣሪ ከሆነው አንዱ ጌታ በስተቀር የሚመለኩ ነገሮችበሙሉ ባጢል (ሐሰት) ናቸው፡፡አምልኮ የሚገበው ከጉድለት የጠራውና ከፍ ለለው ለአላህ ብቻ ነው፡፡

አምልኮ የሚገባው ከጉድለት የጠራውና ከፍ ያለው አላህ ብቻ ነው፡፡ ቀልቦች በውዴታ፣ በማላቅ፣ በማክበር፣በመተናነስ፣ ዝቅ በማለት፤ በመፍራት፣ በርሱ ላይ በመመካት ያመልኩታል፡፡ ለልመናም እርሱን ይጠሩታል፡፡ ከአላህ ውጪ ለልመና የሚጠራ የለም፡፡ እርዳታ የሚጠየቀው እርሱ ብቻ ነው፡፡ በርሱ ካልሆነ በማንም መመካት አይቻልም፡፡ ለርሱ ካልሆነ ለማንም አይሰገድም፡፡የአምልኮ እርድ ለርሱ ካልሆነ ለማንም አይታረድም፡ አምልኮ የተባለን በሙሉ ለርሱ ብቻ ማጥራት ግዴታ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል፡፡ “አላህን ሃይማኖትን ለርሱ ብቻ አጥሪዎች ቀጥተኞች ሆነው ሊገዙት፣ ሶላተንም አስተካክለው ሊሰግዱ ዘካንም ሊሰጡ እንጅ ያልተዘዙ ሲኾኑ (ተለያዩ)፡፡” (አል-በይናህ፡4)

ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም የሚለው ቃል በማረጋገጥ፥ አላህን ጥርት አድርጎ ያመለከ ሰው፥ ታላቅ የሆነ ደስታን ይጎናፀፋል፡፡ እርጋታና ስክነት ያለው መልካም ህይወት ይኖራል፡፡ አላህን በብቸኝነት ከማምለክ ሌላ፥ ለቀልብ ትክክለኛ የሆነ መረጋጋትን፣እርካታንና ረፍት የሚሰጥ ሌላ ነገር የለም፡፡ አላህ እንዲህ ብሎዋል፡፡ “ከወንድ ወይም ከሴት እርሱ አማኝ ሆኖ በጎን የሠራ መልካም ኑሮን በእርግጥ እናኖረዋለን…”(አል-ነሕል፡97)

“ከአላህ በስተቀር በእውነተ የሚመለክ አምላክ የለም” የሚለው ቃል መሠረቶች

١
የመጀመሪያው ምሰሶ፡- (አምላክ የለም)የምለው ነው። ይህም ከአላህ ውጭ ላለው አምልኮ እንዳይደረግ መቃወም ነው፣ ሽርክን ማጥፋት፣ ከአላህ ውጭ ባለው በምመለክ በነገሩ ሁሉ መካድ የግድ ነው። ሰው፣ እንስሳ ፣ ጣዖት ፣ ከዋክብት ፣ ወይም ሌላ ማንኛውንም ነገር ብሆን።
٢
ሁለተኛው ምሰሶ፡- (ከአላህ በስተቀር) ይህ ለአላህ ብቻ መገዛትን ማረጋገጥ እና የሁሉን ቻይ የሆነውን አላህ የአምልኮ ዓይነቶች ሁሉ እንደ ጸሎት፤ ልመና፤ መመካት እና ሌሎችንም ለሱ ብቻ መድረግ ነው።

የአምልኮ ዓይነቶችን በሙሉ ልንሰጥ የሚገባው አንድና አጋር ለሌለው አላህ ብቻ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱን እንኳ ከአላሀ ውጪ ላለ ነገር አሳልፎ የሰጠ ከሃዲ ይሆናል፡፡ አላህ እንዲሀ ይላል …“ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ ለርሱ በርሱ ማስረጃ የሌለውን የሚግገዛ ሰው ምርመራው ጌታው ዘንድ ብቻ ነው፤ እነሆ ከሀዲዎች አይድኑም፡፡” (አል-ሙእሚን፡117)

ከአላሀ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም የሚለው ቃል ትርጓሜና መሠረቶች እንዲህ በሚለው የአላህ ቃል ውስጥ ተገልጿል… “በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡”(አል-በቀራህ፡256) በዚህ የአላህ ቃል ውስጥ “በጣዖትም የሚክድ” የሚለው ቃል የመጀመሪያ መሠረት የሆነውን “አምላክ የለም” የሚለውን ቃል ሲሆን ያረጋገጠው “በአላህ የሚያምን” የሚለው የጌታችን ቃል ደግሞ ሁለተኛ መሠረት የሆነውን ከአላህ በስተቀር የሚለውን ቃል የረጋግጥልናል፡፡

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር