መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የሶላት ቅድመሁኔታዎች እና ድንጋጌዎች

ሶላት ከነሱ ውጪ ተቀባይነት የሌላቸው ቅድመ ሁኔታዎች ስላሉት ሙስሊሙ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች ማወቅ አለበት። በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ ሶላት ቅድመ ሁኔታዎች ፣ብያኔዎች እና ደረጃዎች ይማራሉ ።

  • የሶላት ቅድመ ሁኔታዎችን ማወቅ።
  • የሶላት ብያኔ ማወቅ።
  • የሶላት መስገጃ ቦታ ደንብ ማወቅ፡፡

ለሠላት ሊሟሉ የሚገቡ መስፈርቶች

1 ከሐደስና ከነጃሳ መጥራት፡፡

ከሐደስና ከነጃሳ መጥራት አብደላህ ቢን ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዳስተላለፉት፡- የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፡- “ሶላት ያለ ጦሃራ አይቀበልም” (ሙስሊም 224)።

2 ሀፍረተ ገላን መሸፈን

ሀፍረተ ገላን በአጭርነትና ወይም በስስነት የሰውነት ክፍሎችን የማያጋልጥና የማያሳይ በሆነ ልብስ መሸፈን የግድ ነው፡፡

የወንድ ሀፍረተ ገላ

ከእምብርቱ እስከ ጉልበቱ ድረስ ነው፡፡

የሴት ሀፍረተ ገላ በሶላት ውስጥ

ለሴት፡ ሰላት ለመስገድ የደረሰች ሴት ሀፍረተ ገላ ከፊቷና ከመዳፎቿ በስተቀር ሰውነቷ በሙሉ ነው፡፡ከዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፈችው፡- ነቢዩ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- “አላህ ለወር አበባ የደረሰች ሴት ሶላትን (ማለትም የአዋቂን) በህጃብ እንጂ አይቀበልም። ” (አቡ ዳዉድ 641፣ ቲርሚዚይ 377)

አላህ (ሱ.ወ)፡- «የአደም ልጆች ሆይ (ሀፍረተ ገላችሁን የሚሸፍኑትን) ጌጦቻችሁን በመስገጃው ሁሉ ዘንድ ያዙ፡፡» ይላል፡፡ (አል አዕራፍ 31) ሀፍረተ ገላን መሸፈን ከመጌጥ ትንሹ ደረጃ ነው፡፡ ‹‹በመስገጃው ሁሉ›› ማለት በየሠላቱ ማለት ነው፡፡

3 ወደ ቂብላ መቅጣጨት ወይም መዞር

አላህ (ሱ.ወ)፡- «ከየትም (ለጉዞ) ከወጣህበት ስፍራ ፊትህን ወደ ተከበረው መስጊድ አቅጣጫ አዙር፡፡» ብሏል፡፡ (አል በቀራ 149)

የሙስሊሞች የስግደት አቅጣጫ ምንድነች?

የሙስሊሞች የስግደት አቅጣጫ የተከበረው ካዕባ ነው፡፡ እሷን የገነባት የነብያት አባት የሆነው ኢብራሂም(ዐ.ሰ) ነው ፡፡ ነብያት ወደርሷ የአምልኮ ጉዞ (ሐጅ) አድርገዋል፡፡ እርሷ የማትጠቅም የማትጎዳም ድንጋይ እንደሆነች እናውቃለን፡፡ ግን አላህ (ሱ.ወ) ሙስሊሞች በሙሉ ወደ አንድ አቅጣጫ በመዞር አንድ እንዲሆኑ፣ ስንሰግድ ወደርሷ እንድንዞር ወይም እንድንቅጣጭ አዞናል፡፡ ስለሆነም፣ ወደ ካዕባ በመዞራችን የአላህ ባርነታችንን እንገልፅበታለን፡፡

ወደ መካ አቅጣጫ መዞር

አንድ ሙስሊም ሲሰግድ ካዕባን ፊት ለፊት የሚመለከታት ከሆነ ወደርሷ ፊቱን ማዞር ግድ ነው፡፡ ከርሷ በርቀት የሚገኝ ሰው ደግሞ ወደ መካ አቅጣጫ መዞሩ በቂ ነው፡፡ በሚቅጣጭ ጊዜ ከካዕባ አቅጣጫ ትንሽ ማዘንበሉ ወይም መዞሩ ችግር የለውም፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡- «በምስራቅና በምዕራብ መሐከል ያለ በሙሉ የሠላት አቅጣጫ (ቂብላ) ነው፡፡›› ብለዋል፡፡ (አል ቲርሚዚ 342)

በበሽታ ወይም በሌላ ምክንያት ወደ ካዕባ መዞር ካልቻለስ?

ልክ የተቀሩት ግዴታዎች በመቸገር ምክንያት ግዴታነታቸው እንደሚነሳ ሁሉ፣ በበሽታ ወይም በሌላ ምክንያት ወደ ካዕባ መዞር ላልቻለም ግዴታነቱ ይነሳለታል፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- «አላህንም የቻላችሁትን ያክል ፍሩት፡፡» ይላል፡፡ (አል ተጋቡን 16)

4 የሠላት ወቅት መግባት

ይህ ለሠላት ትክክለኛነት መስፈርት ነው፡፡ ወቅቷ ከመግባቱ በፊት የተሰገደች ሠላት ትክክለኛ አትሆንም፡፡ ከወቅቷ ማዘግየትም የተከለከለ ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- «ሶላት በምእመናን ላይ በጊዜያት የተወሰነች ግዴታ ናትና፡፡» ይላል፡፡ (አል ኒሳእ 103)

ሠላትን በመጀመሪያው ወቅት ላይ መስገዱ በላጭ ነው፡፡በኡሙ ፋርዋ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፈችው፡- የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) ተጠየቁ፡- የትኞቹ ሥራዎች በላጭ ናቸው? እንዲህ ብለዋል፡- “ሶላት በመጀመሪያ ግዜ ላይ መስገድ ነው” (አቡ ዳዉድ 426)።

ሠላትን ማዘግየት ይቻላል?

ሠላትን በወቅቷ መስገድ ግዴታ ነው፡፡ በማንኛውም ምክንያት ቢሆንም ሠላትን ማዘግየት ክልክል ነው፡፡ መሰብሰብ የተፈቀደበት ሁኔታ ስቀር

በእንቅልፍ ወይም በመርሳት ምክንያት ሠላት ያለፈው ሰው ምን ያደርጋል?

በእንቅልፍ ወይም በመርሳት ምክንያት ሠላት ያለፈው ሰው ባስታወሰ ጊዜ ፈጥኖ መስገድ አለበት። አነስ ቢን ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁም እንዲህ ብለዋል፡- የአላህ ነቢይ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- “ሶላትን የረሳ ወይም ከርሷ የተኛ ሰው መካካሸው ስያስተውስ መስገድ ነው።” (ሙስሊም 684)።

የሠላት ግዴታነት

ሠላት፣ በወር አበባና በወሊድ ደም ላይ ያሉ ሴቶች ሲቀሩ በማንኛውም ጤናማ አዕምሮ ባለው፣ ሃላፊነትን ለመሸከም በደረሰ ሙስሊም ሁሉ ላይ ግዴታ ነው፡፡ ሴቶች በወር አበባ ወይም በወሊድ ደም ላይ ሆነው አይሰግዱም፡፡ ከጸዱና ደሙ ከተቋረጠ በኋላም ሠላትን አይከፍሉም፡፡

ለአቅመ አዳምና ሄዋን መድረስ የሚወሰነው ከሚከተሉት ምልክቶች አንዱ ሲሟላ ነው፡፡

١
አስራ አምስት ዓመት መድረስ
٢
በፊት ለፊት ወይም በኋላ ብልቶች ዙሪያ ከርደድ ያለ ጸጉር ማብቀል
٣
በሕልም ወይም በንቃተ ሕሊና የፍቶት ፈሳሸን ማፍሰስ
٤
ለሴት፣ የወር አበባ መታየት ወይም ማርገዝ

አምስቱ የግዴታ ሠላቶችና ወቅቶቻቸው

አላህ (ሱ.ወ) በሙስሊሞች ላይ በቀንና በሌሊት ውስጥ አምስት ሠላቶችን ግዴታ አደርጓል፡፡ እነኚህ ሠላቶች የሃይማኖት ምሶሶዎች ናቸው፡፡ ግዴታነታቸውም እጅግ አጽንዖት የተሰጠው ጉዳይ ነው፡፡ ለነርሱም የሚከተሉትን ወቅቶች አድርጎላቸዋል፡፡

የፈጅር ሠላት፡

የፈጅር ሠላት፡ ሁለት ረካዓ ነው፡፡ ወቅቱ የሚጀምረው ጎሕ ከሚወጣበት ጊዜ ሲሆን፣ በአድማስ ላይ ብርሃን ሲፈነጥቅ ወይም ጨለማ መገፈፍ ሲጀምር ይከሰታል፡፡ የሚያበቃው ደግሞ ፀሐይ ስትወጣ ነው፡፡

የዙህር ሰላት፡

የዙህር ሰላት፡ አራት ረከዓ ነው፡፡ ወቅቱ የሚጀምረው ፀሐይ ከመሐል አናት በምታዘነብልበት ጊዜ ሲሆን የሚያበቃው ደግሞ የእያንዳንዱ ነገር ጥላ ከራሱ ቁመት ጋር ሲስተካከል ነው፡፡

የዐሥር ሠላት፡

የዐሥር ሠላት፡ አራት ረከዓ ነው፡፡ ወቅቱ የሚጀምረው የዙህር ወቅት ካበቃበት ጊዜ ጀምረ ሲሆን ይኸውም የእያንዳንዱ ነገር ጥላ ከራሱ ቁመት ጋር ሲስተካከል ነው፡፡ የሚያበቃው ደግሞ ፀሐይ ስትጠልቅ ነው፡፡ አንድ ሙሰሊም ይህችን ሠላት፣ የፀሐይ ብርሃን ጮራ መድከምና መገርጣት ሳይጀምር ፈጠን ብሎ ሊሰግድ ይገባዋል፡፡

የመግሪብ ሠላት፡

የመግሪብ ሠላት፡ ሦስት ረከዓ ነው፡፡ ወቅቱ የሚጀምረው ፀሐይ ከጠለቀችበትና ፍንጣቂዋ ከአድማስ ላይ ሲወገድ ወይም ሲደበቅ ነው፡፡ የሚያበቃው ደግሞ ከፀሐይ መጥለቅ በኋላ የሚታየው ቀዩ ወጋገን ሲጠፋ ነው፡፡

የዒሻእ ሠላት፡

የዒሻእ ሠላት፡ አራት ረከዓ ነው፡፡ ወቅቱ የሚጀምረው ቀዩ ብርሃን ከጠፋበት ቅጽበት ነው፡፡ የሚያበቃው እኩለ ሌሊት ላይ ነው፡፡ አስቸጋሪ ሁኔታ በሚገጥምበት ጊዜ ጎህ እስኪ ቀድ ባሉት ሰዓቶችም ውስጥ ሊሰገድ ይችላል፡፡

የሠላት ቦታ (ስፍራ)

ኢስላም ሠላት በህብረት ወይም በጀመዓ እንዲፈፀም አዟል፡፡ ለሙስሊሞች መገናኛና መሰባሰቢያ መንገድ ይሆን ዘንድም በመስጂድ ውስጥ እንዲፈፀም አበረታቷል፡፡ ይህን በማድረግ፣በመካከላቸው ወንድማማችነትና ፍቅር ይጨምራል፡፡ ኢስላም የጀመዓ ሠላትን አንድ ሰው ለብቻው ከሚሰግደው ሰላት በብዙ ደረጃዎች የሚበልጥ አድርጎታል፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡- «አንድ ሰው በጀመዓ የሚሰግደው ሠላት በነጠላ ለብቻ ከሚሰገደው ሠላት በሃያ ሰባት ደረጃ ይበልጣል፡፡» ብለዋል፡፡ (አል ቡኻሪ 619/ ሙስሊም 650/ አህመድ 5921)

የሠላት ቦታ ይዘት

ኢስላም፣ ሠላት የሚሰገድበት ቦታ ንጹህ እንዲሆን በመስፈርትነት አስቀምጧል። አላህ (ሱ.ወ)፡- «ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም፣ ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ ስንል ቃል ኪዳን ያዝን፡፡» ይላል፡፡ (አል በቀራ 125)

የነገሮች መስረት ቦታው ንጹህ መሆን ነው

የነገሮች መስረት ንጹህ ነው፤ ነጃሳ ደግሞ ባዕድ/መጤ ነው፡፡ ስለሆነም፣ ነጃሳ ያለበት መሆኑን እርግጠኛ ባልሆንክበት ነገር ላይ ንጹህነትን ትወስናለህ፡፡ በሁሉም ወለል ላይ መስገድ ይቻላል በመስገጃ ወይም ሰሌን ላይ እንጂ አለመስገድ የሚወደድ ተግባር አይደለም፡፡

ለሶላት ቦታዎች ልንከተላቸው የሚገቡ በርካታ ስርዓተ ደንቡች አሉ፡፡ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡

1 በመስገጃ ስፍራ ላይ ሰዎችን አለማስቸገር፡፡ ለምሳሌ፡ የመተላለፊያ መንገድ ላይ መስገድ፣ እንዲሁም ግፊያና መጨናነቅን በሰዎች ላይ የሚፈጥር ስፍራ ላይ መቆም፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሰዎችን ማስቸገርና በነሱ ላይ ጉዳት ማድረስን ሲከለክሉ፡- «መጉዳትም መጎዳትም (በኢስላም) ቦታ የለውም፡፡» ብለዋል፡፡ (ኢብኑ ማጃህ 2340/ አህመድ 2865)

2 በመስገጃ ቦታ ላይ፣እንደ ስዕል፣ ከፍ ያለ ድምጽና ሙዚቃ ያለ፣ ሰጋጅን የሚረብሽና ትኩረቱን የሚበትን ነገር መኖር የለበትም፡፡

3 የመስገጃ ቦታ፣ እንደ ዳንስና ጭፈራ ቤት ያለ፣ አላህን ለማመፅ የተዘጋጀ መሆን የለበትም፡፡ በዚህ መሰሉ ስፍራ ሠላት መስገድ የተጠላ ነው፡፡

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር