መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት ኢድ በዓል

በዓላት ከሚታዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች መካከል ናቸው፣ አላህ ለእያንዳንዱን ህዝብ የተለያዩ በዓላት አድርጓል። በዚህ ትምህርት በእስልምና ስለ በዓላት አንዳንድ ነገሮችን ትማራለህ።

ስለ ሙስሊም በዓላት ማወቅ።ስለ ኢድ ሰላት ባህሪ ማወቅ።ከበዓሉ ጋር የተያያዙ አንዳንድ ህጎች እና ስነ-ስርዓቶችን ማወቅ።

የተባረከው የጾም ፍቺ በዓል

የተባረከው የዒድ በዓላት፣ ከሃይማኖት መገለጫዎች ውስጥ ይመደባሉ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መዲና በመጡበት ወቅት አንሣሮችን ከዓመቱ ቀናት በሁለት ቀኖች ውስጥ ሲፈነጥዙ፣ ሲጫወቱና ሲደሰቱ አግኝተዋቸው ነበር፡፡ እናም፡ ‹‹እነዚህ ሁለት ቀናት የምን ቀኖቻችሁ ናቸው?›› በማለት ጠየቋቸው፡፡ እነሱም፡ ‹‹ከኢስላም መምጣት በፊት- በጨለማው ዘመን እንደሰትባቸው የነበሩ ቀኖች ናቸው፡፡›› በማለት መለሱ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ)፡- ‹‹አላህ እነዚህን ቀናት ከነርሱ በተሻሉ ሁለት ቀናት ተክቶላችኋል፡፡ የእርድ ዕለትና የፍስክ ዕለት›› አሏቸው፡፡ (አቡ ዳውድ 1134) ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፣ በዓላት የሃማኖቶች መገለጫ እንደሆኑ ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹እያንዳንዱ ሕዝብ በዓል አለው፡፡ ይህ ደግሞ በዓላችን ነው፡፡›› (አል ቡኻሪ 909 /ሙስሊም 892)

በዓል በኢስላም

በኢስላም ውስጥ፣ በዓል አንድ የአምልኮ ዘርፍን ስላጠናቀቁ ደስታን የሚገልጹበትና አላህ(ሱ.ወ) ለዚህ አምልኮ ስለመራቸውና ስለገጠማቸው እሱን የሚያመሰግኑበት አጋጣሚ ነው፡፡ በዒድ ቀን፣ የሚያማምሩ ልብሶችን በመልበስ፣ ለከጃዮች መልካም በመዋል በሰዎች ልቦና ውስጥ ደስታን መፍጠር አስፈላጊ እንደሆነ ኢስላም ያስተምራል፡፡ በማንኛውም የተፈቀዱ መንገዶች፣ የሁሉም ልቦና የደስታ ስሜት እንዲሰማውና የአላህን ጸጋ የሚያስታውስ እንዲሆን ማድረግ ተገቢ ነው፡፡

የሙስሊሞች በዓል በዓመት ውስጥ ሙስሊሞች የሚያከብሯቸው ሁለት በዓላት አሉ፡፡ ከሁለቱ ቀናት ውጪ ሰዎች እንደ በዓል አድርገው የሚያከብሯቸውን ቀናቶች ማክበር አይፈቀድም፡፡ እነኚህ በዓላት፡

١
የጾም ፍቺ በዓል (የወርሃ ሸዋል የመጀመሪያ ቀን)
٢
የእርድ በዓል (የወርሃ ዙልሒጃ አስረኛ ቀን)

የበዓል ሠላት (የዒድ ሠላት)፡

የበዓል ሠላት (የዒድ ሠላት)፡ ኢስላም፣ ሙስሊሞች ከሴቶችና ሕፃናት ጋር በመሆን በአንድነት ወጥተው ይህን ሠላት እንዲሰግዱ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ አስተምሯል፡፡ የመስገጃ ጊዜው፣ ፀሐይ ወጥታ የጦር ዘንግ ያክል ከፍ ካለችበት ቅጽበት ጀምሮ ከሰማይ መሐከል እስከምታዘነብልበት ጊዜ ይረዝማል፡፡

የዒድ ሠላት አሰጋገድ

አፈፃፀሙ፡ የዒድ ሠላት ሁለት ረከዓ ነው፡፡ ኢማሙ ሲያሰግድ ቁርኣን የሚያነበው ድምፁን ከፍ አድርጎ ሲሆን ከሠላቱ በኋላም ሁለት ኹጥባዎችን ያደርጋል፡፡ በዒድ ሠላት ‹‹አላሁ አክበር›› የሚለውን ቃል በእያንዳንዱ ረከዓ መጀመሪያ ላይ ደጋግሞ ማለት ያስፈልጋል፡፡ በመጀመሪያው ረከዓ ላይ ፋቲሓን ማንበብ ሳይጀምር በፊት፣ ከመጀመሪያው የሠላት መግቢያ ተክቢራ ሌላ ስድስት ጊዜ ‹‹አላሁ አክበር›› ይላል፡፡ በሁለተኛው ረከዓ ላይ ደግሞ ከመጨረሻው ሱጁድ ሲነሳና ሲቆም ከሚለው ተክቢራ ሌላ አምስት ጊዜ ‹‹አላሁ አክበር›› ይላል፡፡

በቤተሰብ ውስጥ ደስታን ማሰራጨት

በተፈቀዱ መንገዶች ሁሉ በመጠቀም፣ በተቻለ መጠን፣ በቤተሰብ ውስጥ፣ ትልቁንም፣ ትንሹንም፣ ወንዱንም፣ ሴቱንም፣ እንዲደሰትና እንዲዝናና ማድረግ በኢስላም የተደነገገ ተወዳጅ ተግባር ነው፡፡ የሚያምር ልብስ መልበስም እንዲሁ የተወደደ ነው፡፡ በዒድ ቀን መጾም ክልክል ነው፡፡ በዒድ ቀን የሚወደደው፣ በመብላትና በማፍጠር አላህን መገዛት ነው፡፡

በኢድ ዋዜማ ሌሊቱን፣ እንዲሁም ወደ ዒድ ሠላት ሲወጣ፣ ‹‹አላሁ አክበር›› በማለት አላህን ማላቅ

በኢድ ዋዜማ ሌሊቱን፣ እንዲሁም ወደ ዒድ ሠላት ሲወጣ፣ ‹‹አላሁ አክበር›› በማለት አላህን ማላቅ ኢስላም የደነገገው ተግባር ነው፡፡ የዒድ አልፊጥር ሠላት ተሰግዶ ሲያበቃ የተክቢራው ጊዜ ይጠናቀቃል፡፡ ይህ የሚደረገው፣ አላህ(ሱ.ወ) ወደ ጾም በመምራት፣ የተባረከውን የረመዳንን ወር ጾም ለማጠናቀቅ ስላበቃን፣ ለዋለልን ጸጋ እርሱን ለማመስገንና ደስታችንን ለመግለጽ ነው፡፡ አላህ ሱ.ወ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ቁጥሮችንም ልትሞሉ፣ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህንን ደነገግንላችሁ)›› (አል በቀራ 185)

የተክቢራ አባባል፡

‹‹አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላኢላሃ ኢለላህ፤ አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ወሊላሂልሐምድ›› የሚል ነው፡፡ እንዲሁም፡ ‹‹አላሁ አክበሩ ከቢራ ወልሐምዱሊላሂ ከሲራ ወሱብሓነላሂ ቡክረተን ወአሲላ›› ይባላል፡፡

ወንዶች፣ ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ፣ ሰዎችን በማይረብሽ ወይም በማያስቸግር መልኩ ተክቢራን መመላለሳቸው የተደነገገ ተግባር ነው፡፡ ሴቶች ግን ድምፃቸውን ዝቅ ማድረግ አለባቸው፡፡

ከመካ የመስጂደልሀራም ተክቢራ አዳምጥ

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር