መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት በአላህ ጌትነት ማመን

ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ አላህ የሁሉም ነገር ጌታ፣ ፈጣሪው እና ሰጪው ነው።በዚህ ትምህርት ስለ አንድ አምላክ አምላክነት እና ስለ ውጤቶቹ ትማራለህ።

  • የጌትነት ተውሂድን ትርጉም ማወቅ።
  • የጌትነት ተውሂድን ውጤት ማወቅ።

በኃያሉ አላህ ጌትነት የማመን ትርጉም፡-

ኃያሉ አላህ የሁሉም ነገር ባለቤት፣ ፈጣሪና ሲሳይን ሰጪ ነው ብሎ አምኖ መቀበልና እውነት ነው ብሎ በቁርጠኝነት ማረጋገጥ ነው፡፡ በጌትነቱ ማመን ማለት ህይወት የሚሰጠውና የሚነሳው፣ የሚጠቅመውና የሚጎዳው እርሱ ብቻ ነው ብሎ ማመን ነው፡፡የሁሉም ትዕዛዝ ባለቤት እርሱ ነው ማለት ነው፡፡መልካም ነገር ሁሉ በእጁ ነው፡፡ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፡፡ በእነዚህ ሁሉ ነገሮችም ተጋሪ የለውም ብሎ ማመን ነው፡፡ይህ እንግዲህ አላህ በተግባሩ ብቸኛ ነው ብሎ ማረጋገጥ ነው፡፡ ስለዚህ እንደሚከተለው ማመን ያስፈልጋል፡-

በፍጥረተ-ዓለሙ ውስጥ ያሉትን ነገሮች የፈጠረው አላህ ብቻውን ነው ከርሱ ሌላ ፈጣሪ የለም፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል… “አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡” (አል- ዙመር፡62) የሰው ተግባር ግን አንድን ነገር ወደ ሌላ ቅርፅ መቀየር ወይም እርስ በእርሱ ማቆራኘትና የመሳሰሉት እንጂ ከባድና ከምንም ተነስቶ የሚፈጥረው ነገር የለም፡፡ ሙት የሆነውን ነገር ወደ ህይወት ማምጣትም አይችልም፡፡

ለፍጥረታት ሁሉ ሲሳይን የሚሰጠው አላህ ነው፡፡ ከርሱ ውጪ ሲሳይን ሰጪ የለም፡፡ አላህ እንዲህ ይላል “በምድር ላይ ምንም ተንቀሳቃሽ የለችም ምግቧ በአላህ ላይ ቢሆን እንጂ…” (ሁድ፡6)

አላህ የሁሉም ነገር ባለቤት ነው፡፡ ከርሱ ሌላ የነገሮች እውነተኛ ባለቤት የለም፡፡ አላህ እንዲህ ይላል “የሰማያትና የምድር በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ንግሥና የአላህ ብቻ ነው፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡» (አል-ማኢዳህ፡12ዐ)

የሁሉም ነገር አስተናባሪ እርሱ ነው፡፡ ከርሱ ሌላ ነገሮችን የሚየሰተናብር የለም፡፡ እንዲህ ይላል… «ነገሩን ሁሉ ከሰማይ ወደ ምድር ያዘጋጃል፡፡» (አል-ሰጅዳህ፡5)

የ አላህ ማስተናበርና የሰው ማስተናበር

ሰሰው ህይወቱንና ጉዳዮቹን የሚያስተናብረው በተገደበና በተወሰነ መልኩ ነው፡፡ ባለውና በሚችለው ነገር ብቻ ነው የሚያስተናብረው፡፡ ይህ ማስተናበር ደግሞ ውጤታማ ሊሆንም ላይሆን ይችላል፡፡ ከጉድለት የጠራውና የኃያሉ ፈጣሪ ማሰተናበር ግን አጠቃላይ ነው፡፡ ከርሱ ቁጥጥር የሚወጣ አንዳችም ነገር የለም፡፡ ያለማንምና ያለምንም ተቃውሞ ያሻውን ፈፃሚ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል “ንቁ፤ መፍጠርና ማዘዝ የርሱ ብቻ ነው፤ የዓለማት ጌታ አላህ (ክብሩ) ላቀ፡፡» (አልአዕራፍ፡54

በአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ዘመን የነበሩ አረብ አጋሪዎች በአላህ ጌትነት ያምኑ ነበር፡-

በአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ዘመን የነበሩ ከሃዲያን አላህ፥ ፈጣሪ፣ ንጉሥና አስተናባሪ መሆኑን ያምኑ ነበር፡፡ ይህ እምነታቸው ግን ወደ እስልምና እንዲገቡ አላደረጋቸውም… “ሰማያትንና ምድርንም የፈጠረ ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በእርግጥ አላህ ነው ይላሉ፡፡” (ሉቅማን፡25) አላህ የአለማት ጌታ መሆኑን፣ ፈጣሪ፣ ባለቤትና አስተናባሪ መሆኑን ያረጋገጠ ሰው፣ አላህን በብቸኝነት ሊያመልክ ይገባዋል፡፡ የአምልኮ ተግባራትን ያለማንም ተጋሪ ለርሱ ብቻ ማዋል ይኖርበታል፡፡

አንድ ሰው የፍጥረተ-ዓለሙ ፈጣሪ፣ አስተናባሪ፣ ህይወት ሰጪና ነሺ አላህ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ የአምልኮ ዓይነቶችን ከርሱ ውጪ ላሉ ነገሮች ማዋል በጣም የማያስገርም ነገር ነው፡፡ ይህ አስጠያፊ በደልና ታላቅ ወንጀል ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ሉቅማን ልጃቸውን ሲመክሩ እንዲህ ያሉት “… ልጄ ሆይ! በአላህ (ጣዖትን) አታጋራ፤ ማጋራት ታላቅ በደል ነውና ያለውን (አስታውስ)፡፡” (ሉቅማን፡13)

የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) አላህ ዘንድ ታላቅ ወንጀል ምን እንደሆነ ሲጠየቁ “አላህ ፈጥሮህ ሳለ ለርሱ ተጋሪን ማድረግህ ነው፡፡” በማለት መልሰዋል፡፡ (አል-ቡኻሪ፡4207 ሙስሊም፡86)

በአላህ ጌትነት ማመን ቀልብን ያረጋጋል፡-

አንድ የአላህ ባሪያ በእርግጠኝነት የሚያውቅ ከሆነ፥ ከኃያሉ አላህ ውሳኔ ውጭ ሊሆን የሚችል ፍጡር እንደሌለ ይገነዘባል፡፡ ምክንያቱም የፍጥረታት ሁሉ ባለቤት አላህ ሲሆን ከጥበቡ ጋር በሚስማማ መልኩ እንዳሻው የሚያደርጋቸው እርሱ ነው፡፡የሁሉም ፈጣሪ እርሱ ነው፡፡ ከአላህ ውጭ ያለው ፍጥረት ሁሉ የተፈጠረና ፈጣሪው ወደ ሆነው አላህ ፈላጊ ነው፡፡ ነገሮች ሁሉ በአላሀ እጅ ናቸው፡፡ ከርሱ ውጭ ፈጣሪ የለም፡፡ ከርሱ ውጭ ሲሳይን ሰጭ የለም፡፡ ከርሱ ሌላ ፍጥረተ-ዓለሙን የሚያስተናብር የለም፡፡ ያለርሱ ፈቃድ የምትንቀሳቀስ ቅንጣት ነገር የለችም፡፡ ያለርሱ ትዕዛዝ የምትቆምም የለችም፡፡ይህ እምነት ያለው ሰው ቀልቡ በአላህ ላይ ብቻ ይንጠለጠላል፡፡ እርሱን ብቻ ይጠይቃል፣ ከርሱ ብቻ ይፈልጋል፡፡ በሁሉም የህይወት ጉዳዩ የሚመካው በርሱ ላይ ብቻ ይሆናል፡፡

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር