መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የልጆች መብት

በዚህ ትምህርት ውስጥ ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያላቸውን መብት ትማራላችሁ።

1 አሏህ ለወላጆች ልጆችን በመስጠት በእነሱ ላይ ያደረገውን ፀጋ ታውቃላችሁ።2 ልጆችን በማሳደግ ዙሪያ ከሸሪአ ጋር የተያያዙ ጠቃሚ ነገሮችን ታውቃላችሁ።3 ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያላቸውን መብቶች ታውቃላችሁ።

አሏህ በወላጆች ልብ ውስጥ ዘርን የመተካት ፍላጎትን አድርጓል። ይህ ምኞት የአባታችን አደም እና የእናታችን ሐዋ ምኞትም ነበር። አሏህ እንዲህ አለ፡ "እሱ ያ ከአንዲት ነፍስ (ከአደም) የፈጠራችሁ ከእሷም መቀናጆዋን (ሐዋን) ወደ እሷ ይረካ ዘንድ ያደረገ ነው። በተገናኛትም ጊዜ ቀላል እርግዝና አረገዘች። ፅንሱን ይዛ ተሸከመች። በከበደችም ጊዜ "ደግ ልጅ ብትሰጠን በእርግጥ ከአመስጋኞች እንሆናለን ሲሉ ጌታቸው አሏህን ለመኑ።" (ሱረቱል አዕራፍ 189) ይህ ምኞታቸው በተሳካ ጊዜ ውለታው እና ፀጋው የመጣው ከአሏህ ነውና ልያመሰኙት ግድ ይላል።

ዘርን ከመተካት እና ከእሱ ጋር ተያያዥ ስለሆኑ ጉዳዮች እስልምና ልዩ ትኩረት ያደርጋል። ይህን ከሚያመላክቱ ነገሮች መካከል አሏህ በቁርአኑ ውስጥ የሰማያት እና የምድር ንግስና የእሱ እንደሆነ ከተናገረ በኋላ ስለ ልጆች እና አሏህ በእነሱ ላይ ስላደረገው ፀጋ የተናገረው ነው። አሏህ እንዲህ አለ፡ "የሰማያት እና የምድር ንግስና የአሏህ ነው። የሚሻውን ይፈጥራል። ለሚሻው ሰው ሴት ልጆችን ይሰጣል። ለሚሻውም ሰው ወንድ ልጆችን ይሰጣል። ወይም ወንዶች እና ሴቶች አድርጎ ያናዳቸዋል። የሚሻውንም ሰው መካን ያደርገዋል። እሱ ሁሉን አዋቂ ቻይ ነውና።" (ሱረቱ አሹራ 49-50) በሌላ በኩል ደግሞ አሏህ ልጆች የዚህ አለም ጌጦች ናቸው ይላል። አሏህ እንዲህ አለ፡ "ገንዘብ እና ልጆች የዚህ አለም ህይወት ጌጦች ናቸው።" (ሱረቱል ካህፍ 46)

ሸሪአ ለልጆች አስተዳደግ እና ለትምህርታቸው ትልቅ ትኩረት ይሰጣል። ምክኒያቱም የወደፊቱ ኡማ ምሰሶዎች ናቸውና። በደግነታቸው ምድር ላይ አሏህን በሚያስደስት መንገድ አሏህን ማገልገል እና መገዛት እንዲቀጥል ያደርጋሉ። አሏህ እንዲህ አለ፡ "እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ድንጋዮች ከሆነች እሳት ጠብቁ።" (ሱረቱ ተህሪም 6) አሊ (ረ.ዐ) እንዲህ አለ፡ የዚህ ትርጉም ስርአት አስይዟቸው አስተምሯቸው ማለት ነው። ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ሁለት ሴት ልጆችን እስኪያድጉ (እስኪጎረምሱ) ድረስ በደንብ ያሳደገ ሰው፤ ጣቶቻቸውን አጠላልፈው እያሳዩ እሱ እና እኔ በትንሳኤዋ ቀን በጣም እንቀራረባለን አሉ።›› (ሙስሊም 2631)

ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያላቸው መብት

١
1 ቁሳዊ መብቶች
٢
2 የግብረገብ መብቶች

ቁሳዊ መብቶች

እነዚህ መብቶች መጠለያ ቤት ፣ ምግብ ፣ መጠጥ ፣ ልብስ ፣ የጤና ወጭዎች እና ሌሎች ለልጆች ጥቅም የሚሰጡ ወጭዎችን ሁሉ መሸፈንን ይይዛል። አባት ይህን ማድረግ በቻለ ጊዜ እነዚህን መብቶች የሚወጣው እሱ መሆን አለበት።

የግብረገብ መብቶች

ወላጆች መፈፀም ካለባቸው የልጆች የሞራል መብቶች መካከል በእስለምና ሃይማኖት አስተምህሮ መሰረት ጥሩ አድርጎ ተንከባክቦ ማሳደግ ነው። ሆኖም ቅዱስ ቁርአን ፣ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሱናን እና የህይወት ታሪካቸውን እንዲማሩ ማድረግ ያስፈልጋል። በእስልምና አስተምህሮ መሰረት እንዲያድጉ ፣ የታዘዙትን እንዲፈፅሙ ፣ የተከለከሉትን እንዲከለከሉ እና መልካም ባህሪ እንዲላበሱ ማድረግ አለባችሁ። ይህ ሁሉ አሏህ እና መልዕክተኛውን በመውደድ ፣ ሃይማኖቱን እና ህጉንም በመውደድ መሆን አለበት።

እዝነት እና ርህራሄ በልጆች አስተዳደግ ላይ ጥልቅ የሆነ ተፅዕኖ አለው። ሆኖም በህይወት ውስጥ ባህሪያቸው ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሮ የሚያበላሻቸው መሆን የለበትም። በሌላ በኩል ደግሞ ለልጆች አለማዘን እና ርህራሄ የሌለው መሆን ፣ እነሱን መበደል ፣ ያለ አግባብ መግረፍ ወ.ዘ.ተ አዕምሯቸው ላይ ከፋት እንዲጫር እና አመፀኞች ፣ ውለታቢሶች ፣ መጥፎ ባህሪ የተላበሱ እና ግራ የተጋቡ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል።

ከሞራል መብቶች መካከል አክብሮት ፣ መረጋጋት ፣ ሰላም እና መዋደድ ፣ መተዛዘን እና መደጋገፍ በቤተሰብ ውስጥ መስፈን አለበት። ወላጆች ወይም የቅርብ ዘመዶች ዘወትር መጨቃጨቅ እና መነታረክ የለባቸውም። ምክኒያቱም ልጆቹ ላይ የራሱ የሆነ ተፅእኖ ያሳድራል። የተጨናነቀ እና ሸህም የሆነ ህይወት እንዲኖሩ ያደርጋቸዋል።

ከሞራል መብቶች መካከል፡ ወላጆች ለልጆቻቸው ጥሩ ጓደኛ እንዲኖራቸው ማድረግ ይኖርባቸዋል። መጥፎ እና የሚኮነን ባህሪ እና ልማድ ያለቸው ሰዎች ጋር እንዲደባለቁ መፍቀድ የለባቸውም። ምክኒያቱም ይህ የእነሱ ባህሪ ላይ ተፅዕኖ ያሳድርባቸዋል። መጥፎ ባህሪያቸው ወደ እነሱ ይጋባባቸዋልና ነው።

ምክር ፣ ማሳሰቢያ እና መመሪያ

አባቶች እና እናቶች የወንድ ልጃቸውን እና የሴት ልጃቸውን ሁኔታ ፣ ባህሪያቸውን እና ድርጊታቸውን መከታተል እና መቆጣጠር አለባቸው።አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ደግሞ ምክር በመለገስ እና መመሪያ በመስጠት ጣልቃ መግባት ይኖርባቸዋል። ነገርግን በሚያደርጉት ነገር መካከለኛ መሆን አለባቸው። ሆኖም የሚሰጡት ምክር ወይም መመሪያ እድሚያቸውን ያገናዘበ እንጅ የተንዛዛ የማያቋርጥ ፣ በጣም ትንሽ ወይም በጣም ትልቅ መሆን የለበትም። ይህም ልጁ ምክሩን በማድመጥ እንዲዝል ፣ እንዲሰለች ሚያደርገው ሲሆን ወደ ስራ ለቀየርም ቸልተኛ እንዲሆን ያደርገዋል። ስለዚህ አባቱ እና እናቱ መቼ እና እንዴት ምክር መለገስ እና መመሪያ መስጠት እንዳለባቸው ጊዜ እና ቦታ መምረጥ አለባቸው።

ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያላቸው መብት

١
1 የልጆች መብት የሚጀምረው ከመወለዳቸው በፊት ጥሩ ባል እና ጥሩ ሚስት በመምረጥ ነው።
٢
2 የልጆች የመፈጠርና በህይወት የመኖር መብት
٣
3 የልጆች የትውልድና ዘር መብት
٤
4 ልጆች የእናታቸውን ጡት የመጥባት
٥
5 ተገቢ እና ጥሩ ስም የማግኘት መብት
٦
6 አቂቃ የማግኘት መብት
٧
7 ጥሩ እንክብካቤ የማግኘት መብት
٨
8 ከወላጆቻቸው ዱአ የማግኘት መብት

ጥሩ ባል እና ጥሩ ሚስት መምረጥ

አንድ ወንድ ለልጆቼ ጥሩ እናት ትሆናለች ብሎ ያሰባትን ሚስት መምረጥ አለበት። አንዲት ሴት ደግሞ ለልጆቼ ጥሩ አባት ይሆናል ብላ የምታስበውን ባል መምረጥ አለባት።

የልጆች የመፈጠርና በህይወት የመኖር መብት

١
1 የሸሪአ ህግ ልጆችን በማንኛውም መንገድ መግደል ከልክሏል። ይህ በጃሂልያ ዘመን ሰዎች ድህነትን በመፍራት ያደርጉት የነበረ ተግባር ነው።
٢
2 የሸሪአ ህግ በዘላቂነት ልጅ አለመውለድን ከልክሏል።
٣
3 የሸሪአ ህግ ልጅ ማስወረድን ከልክሏል እንድሁም ፅንሱ ውስጥ ነፍስ ከተዘራበት በኋላ በተለያየ መልኩ ፅንሱን ማጨናገፍም ክልክል ነው።

የልጆች የዘርና ትውልድ መብት

የልጁ መብት የሚገባው ለአባቱ ነው። ምክኒያቱም ከልጆች የቁሳዊ እና የሞራል መብት ጋር የተያያዘ ነውና። አንድ ሰው ልጁን ያለመቀበል ወይም የመካድ መብት የለውም፤ ለጥርጣሬው በቂ ማስረጃ ኖሮት ካልሆነ በቀር።

ልጆች የእናታቸውን ጡት መጥባት ሃቅ አላቻው

የእናት ጡት መጥባት ብዙ የጤና ፣ የሥነ-ልቦና እና የማህበራዊ ህይወት ጥቅሞች አሉት። አሁን ላይ ያለው ዘመናዊው ሳይንስ ይህን ያረጋግጣል። ለልጁ ጤና ፣ በሽታን ለመቋቋም ፣ ለጥሩ የስነልቦና እና የአዕምሮ እድገት በጣም አስፈላጊ እና የተሟላ ነው። በዚህም ምክኒያት ወደ ፊት ስን-ልቦናው ፣ የማሰብ አቅሙ እና ባህሪው ላይ አወንታዊ ተፅዕኖ አለው። የተለያዩ ሁኔታዎችን እና ስሜቶችን ጤናማ በሆነ መንገድ የመጋፈጥ አቅም ይፈጥርለታል።

ተገቢ እና ጥሩ ስም የማግኘት መብት

ይህ ሁለተኛ ደረጃ መብት አይደለም። ይልቁንም የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሶሃቦቻቸውን ካስተማሩት መሰረታዊ ግዴታዎች ውስጥ አንዱ ነው። መጥፎ እና አወንታዊ ትርጉም ያለው ስም ለልጆቻቸው እንዳይሰጡ አዘዋል። ለዚህም ነበር ሶሃቦች እስልምናን ከተቀበሉ በኋላ ያንዳንዶቹን ስም የቀየሩት። ይህ የሚያመላክተው ስማቸው ስብዕናቸው እና ባህሪያቸው ላይ የራሱ የሆነ ተፅፅኖ ያለው በመሆኑ ነው።

አቂቃ የማግኘት መብት

ይህ አሏህን ለማመስገን አዲስ በተወለደ ልጅ ስም ከልዩ ኒያ (ማሰብ) ጋር እና ቅድመ ሁኔታ ጋር የሚደረግ መስዋዕት ነው። የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ወንድ ልጅ ለአቂቃው ቃልኪዳን ነው። በሰባተኛ ቀኑ መስዋዕት ይደርግለታል ፣ ራሱን ይላጫል እናም ስም ይወጣለታል።›› (አቡዳውድ 2838) እንዲህም ብለዋል፡ ‹‹ሁለት ተመሳሳይ በጎች ለወንድ ልጅ እና አንድ በግ ለሴት ልጅ መስዋዕት ይደረጋል።›› (አቡዳውድ 2834)

ጥሩ እንክብካቤ የማግኘት መብት

ይህ ስነ-ልቦናዊ እና ቁሳዊ እንክብካቤ ሲሆን በወንድ ልጅ እና በሴት ልጅ መካከል ልዩነት የለም። ኑዕማን ቢን በሽር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው እንዲህ አለ፡ አባቴ ስጦታ ሰጠኝ። ነገርግን እናቴ አምራ ቢንት ረውሃ ለዚህ ነገር የአሏህ መልዕክተኛን ምስክር እስኪያደርግ ድረስ አልስማማም አለች። ሆኖም አባቴ ወደ አሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሄደና ከአምራ ቢንት አርዋ ለወለድኩት ልጄ ስጦታ ሰጥቼ ነበር። ነገርግን ለዚህ አንቱ የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ምስክር እንዳደርግ ጠየቀችኝ አላቸው።የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፡ ለሌሎች ልጆችህ ሰጥተሃልን? ሲሉ ጠየቁት። እሱም (አላደረኩም) ሲል አሉታዊ መልስ ሰጠ። የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፡ አሏህን ፍራ፤ ለልጆችህ ፍትሃዊ ሁን አሉት። አባቴም ተመልሶ መጣና ስጦታውን መልሶ ወሰደ።›› (ቡኻሪ 2587 ፣ ሙስሊም 1623)

ከወላጆች ዱአ የማግኘት መብት

የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ያለ ጥርጣሬ ምላሽ የሚያገኙ ሶስት ዱአዎች አሉ፡ የተበደለ ሰው ዱአ ፣ የመንገደኛ ሰው ዱአ እና አባት ለልጁ የሚያደርገው ዱአ ናቸው።›› (ኢብን ማጃ 3862) እንዲህም ብለዋል፡ ‹‹አሏህን በነፍሶቻችሁ ላይ አትለምኑ። ዱአችሁ አሏህ የጠየቁትን በሚሰጥበት ጊዜ ሊገጥም ይችላልና።›› (ሙስሊም 3009)

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር