መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት በሠላት ውስጥ መመሰጥ

በሠላት ውስጥ መመሰጥ የሠላት እውነተኛ መገለጫና አንኳሩ ነው፤ በጣም አስፈላጊ ከሆኑት ባህሪያቷ አንዱ ነው። በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ መመሰጥ ትርጉም እና በሱ ላይ የምያግዙ መንገዶችን ትማራላችሁ

በሶላት ውስጥ መመሰጥ ትርጉም ማወቅ  በመመሰጥ ላይ የምያግዙ መንገዶችን ማወቅ 

በሠላት ውስጥ መመሰጥ

በሠላት ውስጥ መመሰጥ የሠላት እውነተኛ መገለጫና አንኳሩ ነው፡፡ መመሰጥ ማለት፡ አንድ ሰጋጅ፣ በሠላት ውስጥ የተናነሰና እራሱን ዝቅ ያደረገ ሆኖ፣ የሚያነበውን የቁርኣን አንቀጽ፣ ጸሎቱንና ውዳሴን በሕሊናው እያስተነተነ አላህ(ሱ.ወ) ፊት መቆሙ ነው፡፡

መመሰጥ፣ ከአምልኮዎች ሁሉ በላጩና የላቀ የታዛዥነት መገለጫ ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፣ በመፅሐፉ ውስጥ መመሰጥ የምእመናን ባህሪ መሆኑን ትኩረት ሰጥቶ የተናገረው ለዚህ ነው ፡፡አላህ (ሱ.ወ)፡- #ምእመናን ፍላጎታቸውን ሁሉ በእርግጥ አገኙ (ዳኑ) እነዚያ እነሱ በስግደታቸው ውስጥ አላህን ፈሪዎች (የሆኑት); ይላል፡፡ (አል ሙእሚኑን 1-2)

በሠላት ውስጥ መመሰጥ የቻለ ሰው፣ የኢማንና የአምልኮን ጣዕም ማጣጣም ይችላል፡፡ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡- ‹‹የዓይን መርጊያዬ በሠላት ውስጥ ተደርጋልኛለች›› ያሉት ለዚህ ነው፡፡ (አል ነሳኢ 3940) የዐይን መርጊያ ማለት፣ ከዳር የደረሰ ደስታ፣ ስኬትና እርካታን ማግኘት ነው፡፡

በሠላት ውስጥ ለመመሰጥ የሚረዱ መንገዶች

1 አስቀድሞ ለሠላት መዘጋጀት

ዝግጅት ማለት፡ ወንዶች፣ የሚያምር ልብስ በመልበስና ወደ ሠላት በተረጋጋና በሰከነ መንፈስ በመራመድ አስቀድሞ ወደ መስጂድ በመምጣት፣ ከሠላት በፊት የሚከናወኑ ነብያዊ ፈለጎችን በማከናወን የሚረጋገጥ ነው፡፡

2 አዕምሮን የሚያጠምዱ፣ አዘናጊና እንቅፋት የሆኑ ነገሮችን በቅድሚያ ማስወገድ

አንድ ሰው፣ ከፊት ለፊቱ ሐሳቡን የሚሰርቁ ምስሎች፣ ልብ የሚያንጠለጥሉ ጨዋታዎችና ሐሳቡን የሚሰርቁ ድምፆች ባሉበት መስገድ የለበትም፡፡ እንዲሁም፣ ሽንት ቤት መግባት እያስፈለገው፣ ተርቦ ወይም ተጠምቶ፣ ምግብና መጠጥ በቀረበበት ቅጽበት ሠላት መጀመር የለበትም፡፡ ይህ ሁሉ ያስፈለገው ሰጋጁ አዕምሮው ነፃ እንዲሆንና ከባድ ጉዳይን በማስተናገድ እንዲጠመድ ለማድረግ ነው፡፡ ይህ ሲሆን ከፊት ለፊቱ የሚያገኘው ሠላቱን ይሆናል፡፡ ሠላት ደግሞ ከጌታው ጋር የሚነጋገርበት ወሳኝ ነገር ነው፡፡

3 በሠላት ውስጥ መረጋጋት

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሠላትን ሲሰግዱ፣ በሩኩዓቸውም በሱጁዳቸውም ውስጥ፣ እያንዳንዱ መገጣጠሚያቸው ወደ ቦታው እስኪመለስ ድረስ በመረጋጋት ነበር፡፡ ሠላቱን ማሳማር ያልቻለውን ሰውዬ፣ በሠላቱ ውስጥ በሚፈፅማቸው ተግባሮችን በሙሉ በእርጋታና በዝግታ እንዲፈፅም አዘውታል፡፡ መቻኮልን ከልክለዋል፤ችኮላን ከቁራ ውሃ አጠጣጥ ጋር አመሳስለውታል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡- #በስርቆት አደገኛው ሰው ማለት ከሠላቱ ላይ የሚሰርቅ ነው፡፡; ሲሉ፣ ሠሓቦች፡ «ከሰላቱ ላይ የሚሰርቀው እንዴት ነው?» በማለት ጠየቁ፡፡ እሳቸውም፡ #ሩኩዓንም ሱጁዷንም በማጓደል ነው; በማለት መለሱላቸው (አህመድ 22642)

4 ፊት ለፊቱ የሚቆመውን አካል ኃያልነት ማሰብ

በሠላት ውስጥ ሆኖ የፈጣሪን ኃያልነትና ልቅና፣ የነፍሱን ደካማነትና ወራዳነት፣እንዲሁም ጌታው ፊት በመቆም እየተማፀነውና እያናገረው እንደሆነ ያስብ፣ ለርሱ በመዋደቅና በመዋረድ ፈጣሪውን ይለምን፡፡ ከዚህም ባሻገር፣ አላህ (ሱ.ወ) በወዲያኛው ዓለም ለምእመናን ያዘጋጀውንና የደገሰውን፣ እንዲሁም አጋሪያን የሚጠብቃቸውን ቅጣትና ውርደት ያስተንትን፡፡ በወዲያኛው ዓለም ጌታው ፊት የሚቆምበትን ጊዜ ያስታውስ፡፡

አንድ ሰጋጅ በሠላቱ ውስጥ መመሰጥን የሚያገኘው፣ አላህ (ሱ.ወ) እንደሚሰማው፣ የጠየቀውን እንደሚሰጠውና ለልመናው ምላሽ እንደማይነፍገው በሕሊናው መሳል በሚችለው ደረጃ ልክ ነው፡፡

አንድ ሙእሚን በሠላት ውስጥ ሆኖ ይህን በአዕምሮው መሳል ከቻለ፣ አላህ በመፀሐፉ ውስጥ፣ ‹‹ጌታቸውን እንደሚገናኙ እርግጠኞች ናቸው›› ብሎ ከዘከራቸው ሰዎች ይሆናል፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- #(ሠላት) በፈሪዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት፡፡ እነዚያ እነርሱ ጌታቸውን የሚገናኙ እነሱም ወደርሱ ተመላሾች መኾናቸውን የሚያረጋግጡ በኾኑት ላይ እንጅ ከባድ ናት; ይላል፡፡ (አል በቀራ 45-46)

5 የሚነበቡ አንቀጾችን፣ የሠላት ውዳሴና ሙገሳዎችን ማስተንተንና ከነሱ ጋር በሕሊና መጓዝ

ቁርኣን የተወረደው ሊያስተነትኑት ዘንድ ነው፡፡ "ይህ ወዳንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሀፍ ነው አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአዕምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ አወረድነው፡፡;" ሶድ 29

እንዴት ሊያስተነትን ይችላል?

አንድ ሰው የሚያነባቸውን አንቀጾች፣ የሚላቸውን ውዳሴዎችና ዱዓዎች ትርጉም ካላወቀ ሊያስተነትን አይችልም፡፡ ትርጉሙን መረዳት ሲችል፣ በአንድ በኩል እርሱ ያለበትን ሁኔታና ተጨባጭ ነገር፣ በሌላ በኩል ደግሞ የአንቀጾቹን፣ የውዳሴና ልመናዎቹን ትርጉም ማስተንተን ይችላል፡፡ ከዚህም፡ መመሰጥ፣እንዲሁም ለጌታው መዋረድና መዋደቅ ይገኝለታል፡፡ ጥልቅ ስሜት ይሰማዋል፡፡ ምናልባትም ዓይኖቹ ሊያነቡ ይችላሉ፡፡ አንድም አንቀጽ ጫና ሳያሳድርበት አያልፍም፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- #እነዚያም በጌታቸው አንቀጾች በተገሰጹ ጊዜ (የተረዱ ተቀባዮች ኾነው እንጅ ) ደንቆሮችና ዕውሮች ኾነው በርሷ ላይ የማይደፉት ናቸው፡፡; ይላል፡፡ (አል ፉርቃን 73)

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር