መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት ዘካት ትርጉሙና ዓላማዎች

ዘካ የእስልምና ሶስተኛው ምሰሶ ነው።በዚህ ትምህርት ውስጥ ትርጉሙ፣ ስለ አላማው እና ስለ ህግጋቱ ጥበብ ትማራለህ።

የዘከ ትርጉም ማወቅየዘከ ዐላማ ማወቅ ዘካ መውሰድ የሚፈቀድላቸው ወገኖችን ማወቅ 

ምጽዋት

ዘካ የእስልምና ሶስተኛው ምሰሶ ሲሆን ለድሆች፣ ለተቸገሩ እና ለሚገባቸው ሰዎች ከገንዘባቸው የተወሰነ ክፍል በመስጠት ስቃያቸውን ለማቃለል ከአላህ የተጣለበት የገንዘብ ግዴታ ነው።

የዘካ ዓላማ

1 ገንዘብን መውደድ የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ባህሪ ሲሆን፣ ይህ ባህሪው ገንዘቡን በመያዝና በመጠበቅ ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉጉት እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ ኢስላማዊው ሕግ ነፍስ ከዘቀጡ የስስታምነትና ልክ የለሽ የገንዘብ ጥማት ባህሪዎች እንድትጸዳና እንዲሁም ከቁሳቁስ ፍቅርና እንድትላቀቅ ምጽዋትን በግዴታነት ደነገገ፡፡ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ብሏል፡- ‹‹ከገንዘቦቻቸው ስትኾን፣ በርሷ የምታጠራቸውና የምታፋፋቸው የኾነች ምጽዋትን ያዝ፡፡›› (አልተውባ 103)

ምዕዋት መስጠት በማኅበረሰቡ መካከል የመደጋገፍና የመዋደድ መሰረትን ይጥላል፡፡ የሰው ልጅ ነፍስ ውለታ የዋለላትን አካል በመውደድ ላይ የተገራች ናት፡፡ በምጽዋት አማካይነት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አባላት ልክ እንደ አንድ ግንብ ከፊሉ ከፊሉን የሚደግፍና እርስ በርሳቸው የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ሆነው ይኖራሉ፡፡ በመሐከላቸው ስርቆት፣ ዘረፋና ማጭበርበር በብዛት የማይታየውም በዚሁ ምክንያት ነው፡፡

3 በምጽዋት፣ ለዓለማት ጌታ ሙሉ ለሙሉ መማረክና ፍጹም ታዛዥ መሆን ይረጋገጣል፡፡ አንድ ባለ ሃብት፣ ከንብረቱ ላይ ምጽዋትን በሚያወጣ ጊዜ የአላህን ሕግጋት በመተግበርና ትዕዛዙን በመፈፀም ላይ ሲሆን በተሰጠው ጸጋ ላይ የጸጋውን ባለቤት እያመሰገነም ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- ‹‹ብታመሰግኑም እጨምርላችኋለሁ፡፡›› ይለናን፡፡ (ኢብራሂም 7)

ምጽዋትን በመተግበር ማኅበራዊ ዋስትና ይረጋገጣል፣ እንዲሁም በተለያዩ የማኅበረሰቡ ክፍሎች መካከል አንጻራዊ የሆነ የኢኮኖሚ መመጣጠን ይከሰታል፡፡ በተጨማሪም ምጽዋትን ለሚገባቸው የማኅበረሰቡ ክፍሎች መስጠት፣ ሀብት በተወሰኑ የማኅበረሰቡ ክፍሎች ውስጥ የተገደበና የተከማቸ እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ አላህ (ሱ.ወ)፡- ‹‹ከናንተ ውስጥ በሀብታሞቹ መካከል ተዘዋዋሪ እንዳይሆን፡፡›› ይላል፡፡

ምጽዋት የሚሰጠው ለነማን ነው?

ኢስላም ዘካ የሚሰጣቸውን ክፍሎች ገድቦ አስቀምጧል፡፡ አንድ ሙስሊም ከነኚህ ክፍሎች መካከል ለአንዱ ብቻ ወይም ከአንድ በላይ ለሆኑ አካሎች ዘካውን መስጠት ይችላል፡፡ ለሚገባቸው ክፍሎች ሊያከፋፍሉለት ለሚችሉ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበሮች መስጠትም ይችላል፡፡ ዘካን በሀገር ውስጥ ማከፋፈሉ በላጭ ነው፡፡

ዘካ የሚገባቸው ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡

١
ድሆችና ችግረኞች፡ አንገብጋቢና መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላትና ለመሸፈን በቂ አቅም የሌላቸው ናቸው፡፡
٢
ዘካን በመሰብሰብና በማከፋፈል ሰራ ላይ የተሰማሩ የዘካ ሰራተኞች
٣
ከአሳዳሪው እራሱን በመግዛት ነፃ ለመውጣት ለሚጥር ባሪያ፡፡ ይህ ሰው ዘካን በመውሰድ ነፃነቱን ያውጃል፡፡
٤
ብድር ተበድሮ መክፈል ያቃተው ሰው፡ የተበደረው ብድር ለሰዎች በጎ ለመዋልና ለሕዝባዊ ጥቅም ወይም ለግል ጉዳይ ቢሆንም ልዩነት አይኖረውም፡፡
٥
በጦር ግንባር በአላህ መንገድ ላይ ለሚፋለም ጀግና፡ እነኚህ ደግሞ ከሃይማኖታቸውና ከአገራቸው ጠላትን በመመከትና በመጋፈጥ ላይ ያሉ ተዋጊዎች ሲሆኑ ማንኛውም ኢስላምን ለማስፋፋትና ለማሰራጨት፣ የአላህን ቃል ከፍ ለማድረግ የሚሰራ ስራም በዚሁ ስር የሚካተት ነው፡፡
٦
ልቦናቸው ከኢስላም ጋር በመላመድ ላይ ላሉአዲስ ሙስሊሞች፡ እነኚህ፣ ከሃዲያን የነበሩ፣ በቅርቡ ኢስላምን የተቀበሉ፣ ወይም ይሰልማሉ ተብሎ የሚከጀሉና ተስፋ የሚጣልባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ለእነኚህ ዘካ የሚሰጧቸው ግለሰቦች ሳይሆኑ፣ መንግሳታዊ ክፍሎችና ጠቃሚነቱን ሊያገናዝቡና ሊመረምሩ የሚችሉ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ናቸው፡፡
٧
ስንቅ ያለቀበት መንገደኛ፡ ይህ ሰው በአገሩ ከፍተኛ ካፒታል ወይም ንብረት ያለው ቢሆንም ባለበት ሁኔታ፣ ስንቅ ካለቀበት፣ ከተቋረጠበትና ገንዘብ ካስፈለገው ዘካ ይሰጠዋል፡፡
٨
መንገደኛ፡- ከአገሩ ውጪ ሌላ አገር ላይ የታሰረ መንገደኛ፡ ጉዞው ካልተከለከለ መድረሻው የሚደርሰውን ይሰጦታል።

አላህ (ሱ.ወ) ዘካ የሚገባቻን ክፍሎች ሲያብራራ እንዲህ ብሏል፡- ‹‹የግዴታ ምጽዋቶች (የሚከፈሉት) ለድሆች፣ ለሚስኪኖችም፣ በርሷም ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች፣ ልቦቻቸውም (በኢስላም) ለሚለማመዱት፣ጫንቃዎችንም ነፃ በማውጣት፣ በባለ ዕዳዎችም፣ በአላህ መንገድም በሚሰሩ፣ በመንገደኞችም ብቻ ነው፡፡›› (አል ተውባ 60)

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር