መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት ስለ ቅዱስ ቁርኣን

የእነዚህ ርዕሶች ዋና አላማ ተማሪው የቅዱስ ቁርአንን እውነታዎች በአይነ ህሊናው እንዲያይ ፣ ትሩፋቶቹን ፣ ህግጋቱን እና ከእሱ ጋር ሊኖረን ስለሚገባው ምግባር እና ቃላቶቹ እንዴት እንደሚተረጎሙ ወይም እንደሚብራሩ እንዲያው እንዲረዳው የታሰበ ነው።

1 ስለ ቅዱስ ቁርአን እውነታዎች ፣ ስለ ክፍሎቹ እና ስለ ምዕራፎቹ ትማራላችሁ2 የቅዱስ ቁርአን የመሰብሰብ ሂደቶቹን ትማራላችሁ

ቅዱስ ቁርአን

ሃያሉ አሏህ ቁርአን የገለጠው ከፍጡራኖቹ ሁሉ በላጭ ለሆኑ እና ለነብያት መደምደሚያ ለሆኑት ለነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ነው። ቁርአን ለሰው ልጆች ሁሉ መመሪያ እና ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገሪያ ነው። ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "በእርግጥ ከአሏህ ዘንድ ብርሃን እና ገላጭ መጽሐፍ መጣላችሁ። አሏህ ውዴታውን የተከተሉትን ሰዎች የሰላምን መንገድ በእሱ ይመራቸዋል። በፈቃዱም ከጨለማ ወደ ብርሃን ያወጣቸዋል። ወደ ቀጥተኛውም መንገድ ይመራቸዋል።" (ሱረቱል ማኢዳ 15-16)

የቅዱስ ቁርአን ፍች

ቅዱስ ቁርአን ለነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የተገለጠላቸው ተአምራዊ ቃል ነው። ቁርአን በፋቲሃ ጀምሮ በሱረቱ አናስ የሚያበቃ ሲሆን ይህን በማንበብም አሏህ ይመለክበታል።

ቁርአን ክብሩን እና ቱሩፋቱን የሚያመላክቱ ብዙ ስሞች አሉት። ከእነዚህ ስሞች ውስጥ

١
ቁርአን፡ ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "ይህ ቁርአን ወደዚያች ቀጥተኛ ወደ ሆነችው መንገድ ይመራል።" (ሱረቱል ኢስራ 9)
٢
መጽሐፉ፡ ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "ይህ በውስጡ ጥርጣሬ የሌለበት መጽሐፍ ነው።" (ሱረቱል በቀራ 2)
٣
አል-ፉርቃን፡ ሃያሉ አሏህ እንዳለው፡ "ፉርቃንን በባሪያው ላይ ያወረደው (አምላክ) ክብር እና ጥራት ተገባው።" (ሱረቱል ፉርቃን 1)
٤
ዚክር፡ ሃያሉ አሏህ እንዳለው፡ "በእርግጥ ዚክሩን (አስታዋሹን) አወርድነው፤ በእርግጥ እኛም እንጠብቀዋለን።" (ሱረቱል ሒጅር 9)

የቅዱስ ቁርአን መገለጥ

ቁርአን መጀመሪያ ለነብዩ (ሰ.ዐወ) የተገለጠው በረመዷን ውስጥ በለይለቱል ቀደር (በውሳኔዋ ሌሊት) ነው። ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "ያ በእሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩ ገላጭ (አንቀፆች) ሲሆኑ ቁርአን የወረደበት የረመዷን ወር ነው።" (ሱረቱል በቀራ 185)

ቁርአን ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከአሏህ የተገለጠላቸው ከተከበሩ መልአክቶች ውስጥ አንዱ በሆነው በመልአኩ ጅብሪል አማካኝነት ነው። ሃያሉ አሏህ ስለ ቁርአን እንዲህ ይላል፡ "(192) በእርግጥ እሱ (ቁርአን) ከአለማት ጌታ የወረደ ነው። (193) በታማኙ መንፈስ (ጅብሪል) አወረደው። (194) ከአስጠንቀቃቂዎች (ነብያት) ትሆን ዘንድ በልብህ ላይ አወረደው። (195) ግልፅ በሆነ አረብኛ ቋንቋ።" (ሱረቱ አሹአራ ፡ 192-195)

ከቁርአን ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የተገለጠላቸው የመጀመሪያው ራዕይ የሱረቱል አለቅ የመጀመሪያዎቹ አምስት አንቀፆች ናቸው። ተከታዩ የአሏህ ንግግር ነው። "(1) በዚያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ። (2) የሰውን ልጅ ከአለቅ (ከረጋ ደም) በፈጠረው ጌታህ ስም። (3) አንብብ! ጌታህ በጣም ቸር ሲሆን (4) ያ በብዕር ያስተማረ። (5) የሰው ልጅ ያለወቀውን ሁሉ ያሳወቀ በሆነው።" (ሱረቱል አለቅ 1-5)

ከዚያ በኋላ ቁርአን መካ እና መዲና ውስጥ እንደነበረው ነባራዊ ሁኔታ እና የሁነቶች ክስተት ጋር በተያያዘ እና በተለያዩ ጊዜያት በሃያ ሶስት አመታት ውስጥ ለነበዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተገለጠ።

ኢብን አባስ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው እንደህ አለ፡ ‹‹ቁርአን በአንድ አረፍተ ነገር ወደ ሰማኡ ዱንያ (ወደዚህ አለም ሰማይ) የወረደው በለይለቱል ቀድር (በውሳኔዋ ሌሊት) ነው። ከዚያም በኋላ በሃያ ሶስት አመታት ውስጥ ተገለጠ።›› (አልበይሃቂ፡ ስሞች እና ባህሪያት 497)

የቅዱስ ቁርአን ምዕራፎች

የቅዱስ ቁርአን ምዕራፎች 114 ናቸው። ሆኖም የመጀመሪያው ምዕራፍ አል-ፋቲሃ ሲሆን የመጨረሻው ምዕራፍ ደግሞ አል-ናስ ነው።

የመካ እና የመዲና ምዕራፎች

١
የመካ ምዕራፎች 86 ሲሆኑ የተገለጡትም ነብዩ (ሰ.ዐወ) ወደ መዲና ከመሰደዳቸው በፊት ነው።
٢
የመዲና ምዕራፎች 28 ሲሆኑ የተገለጡትም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከተሰደዱ በኋላ ነው።

የቁርአን ክፍሎች 30 ሲሆኑ ሂዝቡ ደግሞ 60 ናቸው።

የቁርአን ጽህፈት እና አሰባሰብ

የቁርአን ጽህፈት እና አሰባሰብ ሶስት ደረጃዎች አሉት።

የመጀመሪያው ደረጃ፡ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘመን

በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘመን ትኩረቱ የነበረው ከመፃፍ ይልቅ ሽምደዳ ላይ ነው። ለዚህ ምክኒያቱ ደግሞ የመሸምደድ አቅማቸው እና ለመሸምደድ የነበራቸው ፍጥነት ጠንካራ በመሆኑ ፣ የጽሐፊዎች እና የመፃፊያ ዘዴ ባለመኖሩ ምክኒያት በመጽሐፍ መልክ አልተሰበሰበም ነበር። ነገርግን አንድ አንቀፅ በሰሙ ጊዜ ይሸመድዱ እና ባገኙት የዘንባባ ዛፍ ጉማጅ ፣ ብራና እና ድንጋይ ላይ ይፅፉ ነበር።

ሁለተኛው ደረጃ፡ በአቡበክር (ረ.ዐ) ጊዜ

በሂጅራ በአስራ ሁለተኛው አመት በየማማ ጦርነት ጊዜ ብዙ ቃሪኦች (አንባቢዎች) በመገደላቸው ምክኒያ እና ቁርአን እንዳይጠፋ በማሰብ ቁርአኑ እንዲሰበሰብ አቡበክር (ረ.ዐ) አዟል።

ዘይድ ኢብኑ ሳቢት(ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው እንዲህ አለ፡ ‹‹የየማማ ሰዎች (በሙሰይሊማ) በተገደሉ ጊዜ አቡበክር (ረ.ዐ) መልዕክት ላከብኝ። እኔም ወደ እሱ ሄድኩ። እናም ኡመር ኢንኑ ኸጧብ ከእሱ ጋር ተቀምጦ አገኘሁት። አቡበክር (ረ.ዐ) እንዲህ አለኝ፡ ‹‹በየማማ የጦር ሜዳ ቁርአን አንባቢዎች ላይ የደረሰው ሞት የከፋ እንደሆነ ኡመር (ረ.ዐ) ነግሮኛል። በሌላ የጦር ሜዳ ተጨማሪ የቁርአን አንባቢዎች እንዳይሞቱ እና ከፍተኛው የቁርአን ክፍል እንዳይጠፋ እሰጋለሁ። ሆኖም ቁርአን እንዲሰበሰብ አቡበክር ትዕዛዝ እንዲያስተላልፍ ሃሳብ አቀረበ። ለኡመርም እንዲህ አልኩት፡ ‹‹የአሏህ መልዕክተኛ ያላደረጉትን አንተ ታደርጋለህን? አልኩት። ኡመርም ያ ጥሩ ነው አለ። አሏህ ለዚህ ነገር ደረቴን እስከከፈተልኝ ጊዜ ድረስ ኡመር ያቀረበውን ሃሳቡን እንድቀበል ጎተጎተኝ። ኡመር የተረዳውን ሃሳብ እኔም መረዳት ጀመርኩ። ከዚያም አቡበክር ‹‹አንተ ጠቢብ ወጣት ነህ፤ በአንተም ላይ አንዳችም ጥርጣሬ የለንም። ለአሏህ መልዕክተኛ የተገለጠላቸውን መለኮታዊ ራዕይ ትፅፋለህ። ሆኖም የተበታተኑ የቁርአን የእጅ ጽሁፎችን አፈላልገህ በአንድ መጽሐፍ አሰባስበው አለኝ። በአሏህ ይሁንብኝ! ከተራራዎቹ አንዱን እንዳንቀሳቅስ ቢያዙኝ ይህን የቁርአን እንዳሰባስብ ካዘዙኝ የበለጠ የሚከብድ አይመስለኝም። ከዚያም ለአቡበክር እንዲህ አልኩት፡ ‹‹የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ያላደረጉትን ነገር እናንተ ታደርጋላችሁን›› አልኩት። አቡበክርም፡ ‹‹በአሏህ ይሁንብኝ ጥሩ ነው›› ሲል መለሰልኝ። አሏህ የአቡበክር እና የኡመርን ደረት እንደከፈተው የእኔንም ደረት እስከከፈተልኝ ድረስ አቡበክር ሃሳቡን እንድቀበል ጎተጎተኝ። ከዚያም ቁርአንን መፈለግ ጀመርኩ። የሱረቱ ተውባን የመጨረሻውን አንቀፅ ከአቢ ኸዛኢም አል-አንሷሪ እንጅ ከእሱ በቀር ከሌላ ሰው ማግኘት እስካልቻልኩበት ጊዜ ድረስ በተለያዩ ነገሮች ላይ በዘንባባ ዛፍ ጉማጆች ፣ በነጭ ድንጋይ ላይ እና በልባቸው ካስቀመጡ (ከሸመደዱ) ሰዎች አሰባሰብኩ። ከዚያም ሙሉ የቁርአን የእጅ ፅሁፍ ቅጅ አቡበክር እስኪሞት ድረስ ከእሱ ጋር ተቀመጠ። ከዚያም ኡመር እስኪሞት ድረስ ከእሱ ጋር ተቀመጠ። ከዚያም የኡመር ልጅ ከሆነችው ሐፍሷ ጋር ተቀመጠ።›› (ቡኻሪ 4986)

ሶስተኛው ደረጃ፡ በኡስማን ኢብን አፋን (ረ.ዐ) ዘመን

በኡስማን ቢን አፋን (ረ.ዐ) የአስተዳደር ዘመን የእስልምና የግዛት ወሰን ተስፋፍቷል። የሁሉም ሐገር ሰዎች ከሶሃቦች መካከል ያስተማሯቸውን የቁርአን የአነባበብ ዘይቤ ተቀበሉ። በቅዱስ ቁርአን የአነባበብ ዘይቤ ብዝሃነት ምክኒያት እና ቅዱስ ቁርአንን ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ያልሰሙ ሰዎች እንዳይሳሳቱም ተፈራ። እናም ሰዎች በሃያሉ አሏህ መጽሐፍ ላይ እንዳይለያዩ ፣ እንዳይጨቃጨቁ እና እንዳይበታተኑ በማሰብ ኡስማን (ረ.ዐ) ሰዎች ሰዎች በአንድ የቁርአን ቅጅ እንዲሰባሰቡ አዘዘ።

አነስ ኢብን ማሊክ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው ሁዘይፋ ቢን አልየማን ወደ ኡስማን መጣ። በአርመን ወረራ ወቅት የሶሪያን ሰዎች ሲዋጋ ፣ አዘርባይጃን ደግሞ ከኢራቅ ሰዎች ጋር ሲዋጉ በነበራቸው የአነባበብ ልዩነት ምክኒያት ኹዘይፋ ፈራ። እናም ኹዘይፋ ለኡስማን እንዲህ አለው፡ ‹‹የሙዕሚኖች አዛዥ ሆይ! አይሁዳዎች እና ክርስቲያኖች እንደተለያዩት ሁሉ ይህ ኡማ በመጽሐፉ ከመለያየታቸው በፊት ተረዳቸው አለው። እናም ‹‹በመጽሐፍ መልክ እናበዛቸው ዘንድ ቅጅውን ላኪልን፤ ከዚያም መልሰን እንልክልሻለን›› ሲል ኡስማን ወደ ሐፍሷ መልዕክት ላከ። ሐፍሷም ወደ ኡስማን ቅጅውን ለከች። ከዛም ዘይድ ቢን ሳቢት ፣ አብዱ ረህማን ቢን አል-ሐሪስ ቢን ሂሻምን በቁርአን ማባዛት ሂደት ውስጥ እንዲካተቱ እና ቁርርአኑን እንዲያባዙ አዘዛቸው።›› (ቡኻሪ 4987)

እስከ አሁኗ ጊዜ ድረስ ቁርአን ያኔ በተሰበሰበበት ሁኔታ እና ሙስሊሞች በተስማሙበት ሁኔታ ተጠብቆ ቆይቷል።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር