መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት የወረርሽኝ ትምህርት በስብከት ውስጥ

ወረርሽኝ እና በሽታ በሚከሰት ጊዜ ሙዕሚኖች (አማኞች) ትኩረት ሊሰጡ የሚችሉባቸው ትምህርቶች እና ስብከቶች አሉ። በዚህ ትምህርት ውስጥ የሙዕሚንን ሰው ኢማን (እምነት) የሚጨምሩ ትምህርቶችን ትማራላችሁ።

ስለ ወረርሽኝ ምንነት ልብን ከሃያሉ አሏህ ጋር ከሚያስተሳስሩ ስብከቶች ጋር ትማራላችሁ።

ወረርሽኝ ሙስሊም የሆኑ እና ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎችን የሚገጥማቸው የአሏህ ውሳኔ ነው። ነገርግን ሙስሊሞችን የሚገጥማቸው ችግር ከሌሎቹ ጋር አንድ አይነት አይደለም። ምክኒያቱም ጌታው ስላዘዘው ከበሽታው ጋር እየታገለ ይታገሳል ፣ ከመከሰቱ በፊት የተፈቀዱ ሰበቦችን በመጠቀም ይከላከላል ፣ ከደረሰበት ደግሞ ታግሶ ያገግማልና ነው።

‹‹በእሱ እንደመሆኑ ለአሏህ ፍትሃዊ መገመትን አላደረጉም።›› (ሱረቱ ዙመር

በማይክሮስኮፕ ብቻ የሚታይ ደካማ ፍጡር በሆነው የኮሮና ቫይረስ ምክኒያት ወረርሽ ተስፋፍቶ አለምን በሙሉ አምሷል። በነፍሶች ላይ ፍርሃት እና ሽብርን አድርሷል። ይህ የአሏህን ሃያልነት እና የሰው ልጆች የደረሱበት ስልጣኔ ላይ ቢደርሱ ፣ የብዙ ቴክኖሎጅ ባለቤት ቢሆኑም ደካማ ፍጡር የመሆናቸው ትልቅ ማሳያ ነው። ሃያሉ አሏህ በሰማያትም ሆነ በምድር ላይ ሁሉን ማድረግ የሚችል አምላክ ነው።

ቀዷ እና ቀደር (የአሏህ ውሳኔ) እውነት ነው!

አሏህ የሻው (የፈለገው) ነገር ሆነ፤ እሱ ያልፈለገው ነገር አልሆነም። ችግሩ እና ወረርሽኙ በአሏህ ፈቃድ ተከስቷል። ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ ‹‹በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ ማንንም አትነካም ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፉ የተመዘገበች ብትሆን እንጅ። ‹‹በእርግጥ ይህ በአሏህ ላይ ገር ነው።›› (ሱረቱል ሐዲድ 22)

በዚህ ፍጥረተ አለም ውስጥ ያለው ክስተት ሁሉ የአሏህ ውሳኔ እና ከመፍጠሩ በፊት በመጽሐፉ ተፅፎ ያለ መሆኑን ሙስሊሞች ያምናሉ። ይህ እምነታቸው በፈሩ እና በተጠራጠሩ ጊዜ እንደገና ያረጋግጣሉ እምነታቸውንም ያጠነክራሉ። የአሏህን ውሳኔ በተከፈተች ልብ ይቀበላሉ።

ግሳፄ እና አሳቢነት

መከራ ወይም ችግር በተከሰተ ጊዜ ከሚስተዋሉ ድክመቶች አንዱ በወቅቱ የሚተላለፉ ዜናዎችን ያለ አሳቢነት እያደመጡ መጨናነቅ እና መፍራት ነው። ከወረርሽኙ መስፋፋት እና ከተከሰተው መከራ ማሳሰብ እና መገሰፅ አሁን አሁን ችላ እየተባለ የመጣ ሱና እና የኢባዳ ስራ ነው። ‹‹ሂላያት አል-አውሊያ›› ውስጥ በአቡደርዳ እንደተገለፀው፡ ‹‹የአንድ ሰአት ተፈኩር (ማስተንተን) ከሌሊት እንቅልፍ ሁሉ የበለጠ ነው።››

መከራ እና ውጣውረዶች ለሙስሊሞች

١
መጥፎ ስራዎች የሚታበሱበት እና ደረጃቸው ከፍ የሚልበት ነው። ሆኖም የአሏህ ባሪያ ኢማን ፣ እርግጠንነት ፣ ትዕግስት (ሶብር) እና ወኔ ያስፈልገዋል።
٢
አስታዋሽ ነው። ሙስሊም ሰው ከነበረበት ስርአት አልበኝነት ፣ መንከራተት እና ከአሏህ መራቅ የሚያነቃው አስታዋሽ ነው።
٣
ቅጣትም ነው። ሙስሊም ሰው በእንደዚህ አይነት ጊዜ መቶበት ፣ ዱአ ማድረግ እና የአምልኮ ተግባራትን ማብዛት አለበት ፣ በመተናነስ እና ለአሏህ እጅ በመስጠት ዱአ ማድረግ ያስፈልጋል።

በመተናነስ እና ለአሏህ እጅ በመስጠት ዱአ ማድረግ

እነዚህ መከራዎች በተከሰቱ ጊዜ ከሚደረጉ የአምልኮ ተግባራት ውስጥ ለአሏህ መተናነስ ፣ እጅ መስጠት እና ዱአ አብዝቶ ማድረግ ነው። እርዳታን መፈለግ እና ከችግሩ ፋታ ለማግኘት መለመን የሚገባው ሃያሉ አሏህ ብቻ ነው። ሃያሉ አሏህ እንዲህ ብሏል፡ "ታዲያ ቅጣታችን በመጣባቸው ጊዜ (አሏህን በመገዛት) አይዋደቁም ኖሯል ግን ልቦቻቸው ደረቁ። ይሰሩት የነበሩትንም ነገር ሰይጣን ለእነሱ አሳመረላቸው።" (ሱረቱል አል አንዓም 43) ቅን የሆነ ዱአ የሰማይን በር ይከፍታል ፣ ግርዶውን ይገልጣል ፣ ርቀትን ይሸፍናል ፣ ከአዛኙ አሏህ ጋር ያቃርባል። "ባሮቼ ስለ እኔ በጠየቁህ ጊዜ እኔ ቅርብ ነኝ በላቸው። የለማኝን ፀሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ።" (ሱረቱል በቀራ 186) ወሃብ ኢብን ሙናቢህ እንዲህ አለ፡ ‹‹መከራ የሚደርሰው ዱአን ሊያወጣ ነው።››

ኢብን ከሲር (ረሂመሁሏህ) እንዲህ አለ፡ ‹‹ቅጣታችን ወደነ እነሱ በመጣ ጊዜ ባይሆን ኖሮ ፣ ዱአ አያደርጉ ነበር።›› ለምን፤ በዚያ ነገር በፈተናቸው ጊዜ ወደ እኛ ይለምናሉ። እኛንም አጥብቀው ይይዛሉ። ‹‹ነገርግን ልቦቻቸው ደረቁ›› ያ ማለት ከሽርክ እና ከሃጢያት መለሳለስ እንኳ የላቸውም።

‹‹እጆቻችሁ በሰሩት (ሃጢያት) ነው›› (አሹራ 30)

ትልቁ እብሪት ከእነዚህ በሽታዎች እና መከራዎች ደህና ነን ብለን ማመናችን እና የምናስበውም ስለመኖር (ስለ ህይወት) ብቻ መሆኑ ነው። መከራ እና ችግር በሃጢያቶቻችን መካከል ያሉ ናቸው። ይህ በብዙ የቁርአን አንቀፅ ተረጋግጧል። ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "በእርግጥ ያገኛችሁ መከራ ባገኛችሁ ጊዜ ‹‹ይህ ከየት ነው›› አላችሁ። እሱ ከነፍሶቻችሁ ነው።" (ሱረቱል ኣለ ኢምራን 165) አሏህ እንዲህ አለ፡ "ከመከራም ያገኛችሁ ነገር እጆቻችሁ በሰሩት ሃጢያት ምክኒያት ነው። ከብዙውም ይቅር ይላል።" (ሱረቱ አሹራ 30)

አሏህ ለባሮቹ ቸር ነው

መከራ እና ችግር በተከሰተ ጊዜ የአሏህ ቸርነት በአማኞች (በሙዕሚኖች) ላይ ይገለጣል። አሏህ ጉዳያቸውን ያቀልላቸዋል ፣ ከክፉ ነገር ይጠብቃቸዋል ፣ የደረሰባቸውን ያቀልላቸዋል ፣ ከክፉ ነገር ይጠብቃቸዋል ፣ የደረሰባቸውን ነገር ያነሳላቸዋል ፣ እንዲታገሱ ያደርጋል። እነሱም አሏህ በወሰነው ነገር ላይ ይደሰታሉ። እንደ ሃያሉ አሏህ ቸርነት ባይሆን ኖሮ ልቦች በብቸኝነት ፣ በፍርሃት እና በስጋት ተሞልተው እራሳቸውን ያከስሙ ነበር።

ይህ አንቀፅ አሰአዲ (ረሂመሁሏህ) ሲያብራራ እንዲህ አለ፡ ‹‹በእርግጥ ጌታየ ለሻው ሰው ሁሉ ቸር ነው።›› ለባሪያው ከማያሰበው ቦታ ፅድቁን እና ቸርነቱን ይለግሰዋል። ከሚጠላው ነገሮች አርቆ ከፍ ወዳለ ደረጃ ይመራዋል።››

በሃያሉ አሏህ መመካት

በአሏህ ላይ መመካት መከራ እና ችግርን ለመጋፈጥ ከሚረዱ ትልቅ መንገዶች ውስጥ አንዱ ነው። ሆኖም መከራው ማለፉ የማይቀር መሆኑን እርግጠኛ ሁኑ። በዙሪያችሁ ላሉ ሰዎች ተስፋ ስጡ ፣ ጭንቀት ፣ ፍርሃትን እና ተስፋ ማጣትን አስወግዱ፤ ያለበለዚያ መከራው ይብዳል እንጅ አይቀልምና። "ከችግር ጋር ምቾት አለ። በእርግጥ ከችግር ጋር ምቾት አለ።" (ሱረቱ ኢንሽራህ 5-6)

‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ተጠንቀቁ››

ህጋዊ እና ሚናው የጎላ ቁሳዊ ሰበቦችን ተጠቅሞ ክፋትን መመከት እና ማባረር አሏህ በዚህ ፍጥረተ አለም ውስጥ ካደረጋቸው ህግጋት አንዱ ነው። መልዕክተኞች እና ደጋግ የአሏህ ባሮች ይህን ተቀብለዋል። ይህ ሙሉ በሙሉ በአሏህ ላይ የመመካት እና ያዘዘውን ነገር የመታዘዝ አንዱ አካል ነው።

የመመካት እውነታ ሰበቡን ለመቀልበስ እየታገሉ በአሏህ ላይ የልብ መመካት ነው። በአሏህ ላይ መመካት እና ሰበቡን መተው ምክኒያታዊነት አልባ መሆን እና ሸሪአንም መስደብ ነው። እንዲሁም ልብ በአሏህ ላይ መመካት ሳይኖራት መንስኤውን ለመቀልበስ መታገል አሃዳዊነትን መክዳት እና በሰበቦች ማሻረክ ነው።

‹‹ይች የዱንያ ህይወት መጠቀሚያ ብቻ ናት›› (ሱረቱ ጋፊር 39)

በአይን ሊታይ የማይችል ፍጡር የአለምን ህዝብ በተድላ ፣ በደስታ ፣ በደህንነት ፣ መረጋጋት እና መተዳደሪያ ገቢ ረብሻቸዋል። ምዕመናን ተዋቸውና እንደው ጤናማ አዕምሮ ያለው ሰው የተረጋጋና ቤቱ አድርጎ መያዝ ፣ በእሱ ላይ መፋለም እና በፍርስራሹ መወዳደርን ይከጅላሉን?

‹‹አማኞች እንደሆናችሁ ፍሩኝ››

ያለ ጥርጥር ይህ ቫይረስ አሏህ ባሮቹን የሚያስፈራራበት እና የሚያስጠነቅቅበት ፣ ከራሳቸው ጋር እንዲመክሩ እንዲያስቡበት ፣ የፍርሃትን እስራት እንዲያድሱ ከሚገፋፋቸው የአሏህ ምልክቶች ውስጥ ነው። ሃያሉ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "ተአምራቶችንም ለማስፈራራት እንጅ አንልክም።" (ሱረቱ ኢስራዕ 59)

የአሏህ ምልክቶችን መፍራት እንዲያንሰራራ ማድረግ

ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መመሪያ አንዱ የአሏህን ምልክቶች መፍራት ነው። አነስ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው እንዲህ አለ፡ ‹‹ከባድ ንፋስ በነፈሰ ጊዜ፤ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት ላይ (ተፅዕኖው) ይታይ ነበር።›› (ቡኻሪ 1034)

‹‹በጨረስክም ጊዜ ቀጥል››

በዚህ አለም ውስጥ የሙስሊሞች ገንዘባቸው ጊዜያቸው ነው። ከገንዘብ እና ከማንኛውም የዋጋ ተመን ሁሉ ይበልጣል። ኢብን አባስ (ረ.ዐ) ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይዞ እንዳወራው እንዲህ አለ፡ ‹‹ብዙ ሰዎች የሚያጧቸው ሁለት በረካዎች አሉ፡ ጤና እና ትርፍ ጊዜ ናቸው። (ቡኻሪ 6412)

ጤናማ አዕምሮ ያለው ሰው ሁልጊዜም ጊዜውን ይጠቀምበታል። ይህ ደግሞ በመከራ እና በችግር ጊዜ የተረጋገጠ ነው። ወደ ሃያሉ አሏህ በሚያቃርበው በማንኛውም ነገር ላይ ጊዜውን ያሳልፋል። ኢብነል ቀይም (ረሂመሁሏህ) እንዲህ አለ፡ ጊዜን ማባከን ከሞትም ይከፋል። ምክኒያቱም ጊዜን ማባከን ከአሏህ ጋር ያለህን ግኙኝነት ሲያቋርጥ ሞት ግን ከዚህ አለም እና ከነዋሪዎቹ ጋር ያቆራርጣል።››

ሽንቂጢ (ረሂመሁሏህ) ይህን የአሏህ ንግግር አስመልክቶ እንዲህ አለ፡ "በጨረስክም ጊዜ ቀጥል" (ሱረቱ ኢንሽራ 7) በአለም ላይ ተንሰራፍቶ ላለው ለባዶነት ችግር መፍትሄ ነው። ሙስሊም ሰው ጊዜውን ባረባ ነገር ላይ አያሳልፍም። ምክኒያቱም ሙስሊም ሰው ለዚህ አለም ወይም ለመጭው አለም ህይወት የሚሆነውን ነገር ይሰራበታልና።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር