መማርዎን ይቀጥሉ

ሎግ ኢን አላደረክም
መማር ለመጀመር፣ እድገትን ለመከታተል፣ ነጥቦችን ለመሰብሰብ እና ወደ ውድድር ለመግባት አሁኑኑ በታ ፕላትፎርም ይመዝገቡ፡ ከተመዘገቡ በኋላ ለሚማሯቸው ርዕሶች የኤሌክትሮኒክስ ሰርተፍኬት ይደርስዎታል።

የአሁኑ ክፍል ::ሞዴል

ትምህርት ብድር

በዚህ ትምህርት ውስጥ ስለ ብድር ሃሳብ እና እሱን በተመለከተ በሸሪአ ህግ ውስጥ ያሉ ሁክሞች (የህግ ብያኔዎች) ትማራላችሁ።

1 ስለ ብድር ሃሳብ ፣ የህግ ብያኔዎቹ እና ተቀባይነት ያለው ለመሆን ሊያሟላቸው ሚገቡ ቅድመ ሁኔታዎችን ትማራላችሁ።2 ተበዳሪው ለአበዳሪው እዳውን በሚመልስለት ጊዜ የሚኖረው ሁኔታ ታውቃለችሁ።

ሃያሉ አሏህ መተዳደሪያን በፍትሁ እና በጥበቡ በሰዎች መካከል ከፋፍሎታል። ከእነሱም መካከል ሐብታም እና ድሃ ፣ አቅመ ደካሞች እና ሚስኪኖች ናቸው። ሰዎች ፍላጎታቸውን ለሟሟላት እርስ በእርሳቸው መበዳደር የተለመደ ነው። ሆኖም የሃያሉ አሏህ ህግ የተሟላ እና ሁሉን አቀፍ በመሆኑ ከብድር ጋር የተያያዙ የተወሰኑ የህግ ድንጋጌዎች አሉት። ሃያሉ አሏህ ብድርን በቁርአን ውስጥ ረዘም ባለው የሱረቱል በቀራ አንቀፅ 282 ላይ ገልፆታል። ይህ አንቀፅ አያቱ ዲን ተብሎ ይጠራል።

የብድር ትርጉም

ለበተጋገዝ ስባል ለሌላ ሰው ተጠቅሞ የሚመልሰው ገንዘብ መስጠት ነው።

የብድር የህግ ብያኔ (ሁክም)

ብድሩ ለአበዳሪው የተወደደ እና ለተበዳሪው የተፈቀደ ነው። ብድር መጠየቅ እንደልመና የተጠላ አይደለም። ምክኒያም ተበዳሪው ገንዘቡን የሚወስደው ሊጠቀምበት እና ፍላጎቱን ሊያሟላበት ነውና። ከዚያም ተመሳሳዩን ገንዘብ ይመልሳል።

ነገርግን ብድሩ ለአበዳሪው ጥቅምን ወይም ትርፍ ገንዘብ ይዞለት የሚመጣ ከሆነ የተከለከለ አራጣ ነው። ገንዘቡን ያበደረው ትርፍ ጨመር አድርጎ እንዲመልስለት ከሆነ ማለት ነው። ልክ እንደዚሁ ሌላ ውል በብድር ላይ እንደ ሽያጭ እና መሰል ነገር ከተጨመረበት የተከለከለ ነው። ምክኒያቱም ብድርን እና ሽያጭን ማቀላቀል አይፈቀድምና ነው።

የብድር ጥበብ

እስልምና ብድርን ፈቅዷል። ምክኒያቱም ለሰዎች መልካም ነገር ይዞ ይመጣል ፣ ጉዳዮቻቸውን እና ጭንቀታቸውን ያቀላል ፣ ችግረኞችን ያፅናናል። እንዶሁም አበዳሪው ወደ አሏህ የሚቃረብበት አንድ መንገድ ነው። የተበዳሪው ፍላጎት ክፍ ባለ ቁጥር የአበዳሪው ሽልማትም ክፍ ያለ ነው።

ብድሩ ትልቅም ሆነ ትንሽ በመፃፍ ወይም የአይን እማኝ በማስመስከር መዝግቦ ማስቀመጥ የተወደደ ነው። ሆኖም ብድሩ የተጠበቀ ይሆን ዘንድ መጠኑን ፣ የሚመለስበትን ሁኔታ እና ቀነ ገደብ መፃፍ አለበት። አበዳሪው በተበዳሪው ሞት ወይም እሱ ራሱ በመርሳት ወይም በክህደት ምክኒያት መብቱን ላለማጣት ዋስትና ይሆነዋል። አሏህ በእዳ አንቀፅ እንዲህ አለ፡ "እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ በዕዳ በተዋዋላችሁ ጊዜ ፃፉት። ፀሐፊም በመካከላችሁ በትክክለ ይፃፍ። ፀሐፊም አሏህ እንደ አሳወቀው መፃፍን እንቢ አይበል። ይፃፍም። ያም በእሱ ላይ እዳ ያለበት ሰው በቃሉ ያፅፍ። ጌታውን አሏህ ይፍራ። ካለበትም እዳ ምንም አያጓድል።" (ሱረቱል በቀራ 282) በዚሁ አንቀፅ አሏህ እንዲህ ይላል፡ "እዳው ትንሽ ወይም ትልቅ ቢሆንም እስከ ጊዜው ድረስ የምትፅፉት ከመሆን አትሰልቹ። እንዲህ ማድረጋችሁ አሏህ ዘንድ በጣም ትክክል ፣ ለምስክርነትም አረጋጋጭ ፣ ላለመጠራጠራችሁም በጣም ቅርብ ነው።" (ሱረቱል በቀራ 282)

የብድር ትክክለኛነት ቅድመ ሁኔታዎች

١
1 ብድሩ የሚፈፀመው ተመሳሳይ ሚና የሚጫወተውን የብድር ሰጭ እና ተቀባይ ቅፅ በመሙላት መሆን አለበት።
٢
2 የሚዋዋሉት ወገኖች፡ አበዳሪው እና ተበዳሪው ማለት ነው። ለአቅመ ኣደም የደረሱ ፣ በአዕምሯቸው ጤነኛ ፣ አሳቢ (አስተዋይ) እና ለመውሰድ እና ለመመለስ ብቁ የሆነ መሆን አለበት።
٣
3 የብድሩ ገንዘብ በሸሪአ የተፈቀደ መሆን አለበት።
٤
4 የብድሩ መጠን ምን ያህል እንደሆነ መታወቅ አለበት።

ከሆነ ሰው ገንዘብ የተበደረ ሰው መልሶ መክፈል አለበት። ለመመለስ ሃሳብ ሳይኖረው የሰዎችን ገንዘብ መውሰድ የተከለከለ ነው። ሆኖም እዳውን የመክፈያ ጊዜ ሲደርስ ለባለቤቱ መመለስ አለበት። አቡ ኹረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ እንዲህ አሉ፡ መልሼ እከፍለዋለሁ ብሎ አስቦ የሰዎችን ገንዘብ የወሰደ ሰው አሏህ በእሱ በኩል መልሶ ይከፍለዋል። ሊገፈው አስቦ የወሰደ ሰው አሏህ እሱን ይገፈዋል።›› (ቡኻሪ 2387)

የተበዳሪው ሁኔታ ብድሩን የሚከፍልበት ጊዜ ስደርስ

١
1 የጊዜ ገደቡ አልቆ የሚከፍለው ነገር ሳይኖረው ሲቀር ። ይህ አይነቱ ተበዳሪ መክፈል ባለመቻሉ ምክኒያት ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው ይገባል። አሏህ እንዲህ አለ፡ "የድህነት ባለቤት የሆነ (ባለዕዳ) ሰው ቢኖር እኪያገኝ ድረስ ማቆየት ነው። በመማር መመፅዋታችሁ ለእናንተ ባላጭ ነው። የምታውቁ ብትሆኑ ትሰሩታላችሁ።" (ሱረቱል በቀራ 280)
٢
2 ሃብቱ ከእዳው በላይ በሚሆንበት ጊዜ። ይህ ተበዳሪ እዳውን መልሶ መክፈል አለበት። ምክኒያቱም ሃብታም ተበዳሪ የእዳውን ክፍያ ከተባለው ቀን ባሻገር ማራዘም አይፈቀድለትምና። አቡ-ኹረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈው የአሏህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ፡ ‹‹ሃብታም ሰው እዳውን ከመክፈል መዘግየቱ ኢፍትሃዊነት ነው።›› (ቡኻሪ 2288 ፣ ሙስሊም 1564)
٣
3 ያለው ገንዘብ ከእዳው ጋር ሲተያይ እኩል በሚሆን ጊዜ እዳውን መክፈል አለበት።
٤
4 ያለው ገንዘብ ከእዳው ያነሰ በሚሆን ጊዜ እና በከሰረ ጊዜ አበዳሪው ከፈለገው ከፊሉን ይከፍላል። ገንዘቡም እንደ እዳው መጠን ከፋፍሎ ይመልሳል።

ገንዘብን ባንክ ውስጥ የማስቀመጥ ሁክም (ብያኔ)

١
1 በሸሪአ ህግ መሰረት የሚሰራ ኢስላማዊ ባንክ ውስጥ ገንዘብን ማስቀመጥ የተፈቀደ ነው፡፡
٢
2 ገንዘብን የወለድ ባንክ ውስጥ ማጠራቀም በተመለከተ ሁለት ጉዳዮች መታሰብ አለባቸው። አንደኛው ወለድ ለማግኘት ሲባል ገንዘብን ማጠራቀም ሲሆን ይህ ያልተፈቀደ ወለድ ነው። ሆኖም ማጠራቀሙ ክልክል ነው። ሁለተኛው ያለ ወለድ የቁጠባ ሂሳብ ውስጥ የሚጠራቀም ገንዘብ ሲሆን ይህም አይፈቀድም። ምክኒያቱም የሚጠራቀመው ገንዘብ ባንኩ በሚያደርገው የወለድ ግብይት ይጠቀምበታልና ነው። እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲፈጠር እና ገንዘቡን የሚያስቀምጥበት ህጋዊ አማራጭ ሳይኖረው ሲቀር ገንዘቡ ይጠፋብኛል ብሎ ወይም ይሰረቅብኛል ብሎ ከፈራ ግዴታ አስፈላጊ በመሆኑ ምክኒያት ገንዘቡን በእንዲህ አይነቱ ባንክ ማጠራቀም ይፈቀዳል።

ተበዳሪው ክፍያውን ቢያዘገይ መቀጫ ገንዘብ መጠየቅ አይፈቀድም። ይህ አራጣ ነው። ልክ እንደዚሁ ባስፈለገ ጊዜ ብድር መውሰድ አይፈቀድም፤ ተበዳሪው እዳውን በጊዜ (በሰአቱ) እከፍለዋለሁ፤ ቅጣቱንም አልከፍልም ብሎ እርግጠኛ እንኳ ቢሆን ማለት ነው። ምክኒያቱም የሚፈፅመው ውለታ የአራጣ ውል ስለሆነ ነው።

እዳን ሲከፍሉ በጎ መሆን

እዳን ሲከፍሉ በጎ መሆን ሲባል ገንዘቡን ሲመልሱ በራሱ ፈቃድ ማንም ሳይጠይቀው ጨመር አድርጎ መመለስ የተወደደ ነው። ምክኒያቱም እዳን የሚከፍሉበት አንድ ጥሩ መንገድ ነውና። በሌላ በኩል ደግሞ ተገዶ ወይም ተጠይቆ ከሆነ ግን የተከለከለ አራጣ ነው።

ትምህርቱን አጠናቅቀሃል


ፈተና ጀምር